Thursday, November 22, 2012

አፍሪቃዉያን ስደተኞች በማልታ

ከሊቢያ ወደጣሊያንና ማልታ የሚፈልሱ አብዛኛዎቹ የኤርትራ ዜጎች የሆኑ የአፍሪቃ ስደተኞች እንቅስቃሴ መቀጠሉን የሮሙ ወኪላችን ተኽለእግዚ ገብረእየሱስ የላከዉ ዘገባ ያመለክታል። በቅርቡ የሜዲትራኒያን ባህርን በጀልባ አቋርጠዉ ወደጣሊያን ያመሩ፤
 250 ስደተኞች ለችግር ተጋልጠዉ በማልታ የባህር ጠረፍ ጠባቂዎች ህይወታቸዉ ተርፏል። ስደተኞቹ ሊቢያ ቤንጋዚ ላይ ለመኖር የሚያስችላቸዉ ህጋዊ ፈቃድ ስለሌላቸዉ ከታሰሩበት ወህኒ ለመዉጣትና ወደአዉሮጳ ሀገሮች ለመጓዝ ገንዘብ እንዲከፍሉ ማንነታቸዉ ባልታወቀ የሊቢያ ዜጎች የተጠየቁ ሲሆን ከፍለዉ የወጡትም ቢሆኑ ቤንጋዚ ላይ በአንዲት ስፍራ ታግተዉ ለመቆየት ተገደዋል። በዚሁ ስፍራም የአንድ ስደተኛ ህይወት አልፏል። በማልታ ባህር ጠረፍ ጠባቂዎች ርዳታ የተረፉት ወገኖች ለተመ የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን ባለስልጣናት እንደገለፁት ለሁለት ቀን የሚሆን ዉሃ ምግብ የሰጧቸዉ ህገወጥ ሰዉ አሸጋጋሪዎች በአነስተኛ ጀልባ ጭነዉ ባህር ላይ ነዉ የለቀቋቸዉ።
ተኽለእግዚ ገብረኢየሱስ
ሸዋዬ ለገሠ
አርያም ተክሌ
ያድምጡ

  «ኤም ፒ 3« 

No comments:

Post a Comment