Tuesday, June 12, 2018

በኦሮሚያ በጭናክሰን ዐስራ አራት ሰዎች በሶማሌ ልዩ ፖሊስ መገደላቸውን አምነስቲ አስታወቀ






ፎቶ፡ አምነስቲ ኢተርናሽናል የተባለው ዓለም አቀፍ ድርጅት ካወጣው ሪፖርት ላይ የተወሰደ ነው።
ከኦሮሚያና ከቤንሻንጉል ክልል የተፈናቀሉ የአማራ ክልል ተወላጆች ምላሽ እንዲሰጣቸው አስፈላጊው ጥበቃም እንዲደረግላቸው አሳስቧል።

በምስራቅ ሐረርጌ በጭናክሰን ወረዳ የሶማሌ ክልል ልዩ ሃይል አባላት በከፈቱባቸው ጥቃት የብዙ ሰው ሕይወት ማለፉን የአካባቢው ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ ገለፁ።
ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተቋም አምነስቲ ኢንተናሽናል ዛሬ ባወጣው መግለጫም ከአርብ ጀመሮ እስከዛሬ ድረስ በሶማሌ ክልል ልዩ ፖሊስ ታጣቂዎች በተፈፀመ ጥቃት ዐሥራ አራት ሰዎች መገደላቸውን አስታውቋል።
ድርጅቱ አርብ ዕለት ባወጣው መግለጫ ደግሞ ከኦሮሚያና ከቤንሻንጉል ክልል የተፈናቀሉ የአማራ ክልል ተወላጆች ምላሽ እንዲሰጣቸው አስፈላጊው ጥበቃም እንዲደረግላቸው አሳስቧል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ዘርን ያማከሉ ጥቃቶችና በተያያዥነት የሚፈጠሩ መፈናቅሎችን ለማስቆም እንዲሁም ዜጎችን ከጥቃት ለመከላከል መሥራት አለበት ብሏል።