Saturday, November 30, 2013

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀ-መንበር ኢ/ር ይልቃል በጀርመን- በስዊዘርላንድ – በሆላንድ – በዋሽንግተን ዲሲ ውይይት ያደርጋሉ



(ኢ.ኤም.ኤፍ) የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀ-መንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት የአውሮፓና የሰሜን አሜሪካ ጉብኝታቸውን ጀምረዋል። ትላንት ኖቨምበር 29 ጀርመን ፍራንክፈርት የገቡት ኢ/ር ይልቃል በመጪዎቹ ቀናት በአውሮፓ ከተሞች ተከታታይ የስራ ጉብኝት እንደሚያደርጉ አስተባባሪ ኮሚቴው በተለይ ለኢ.ኤም.ኤፍ አስታውቋል።
ለጊዜው በደረሰን የስራ ሰሌዳ መሰረት :-
- ቅዳሜ ኖቬምበር 30 በጀርመን ኑረንበርግ ከኢትዮጵያኖች ጋር ውይይት ያደርጋሉ።
- ሰኞ ዲሴምበር 2 በፍራንክፈርት የሚደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ይገኛሉ።
- ዲሴምበር 5 ጄኔቭ ስዊዘርላንድ የሚደረገው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ይሳተፋሉ።
- ቅዳሜ ዲሴምበር 7 በሆላንድ ህዝባዊ ውይይት ያደርጋሉ።
ከአውሮፓ ቆይታቸው በኋላ ወደ ዋሺንግተን ዲሲ በመጓዝ በዲሴምበር 30 አርሊንግተን በተዘጋጀው ስብሰባ ከፕ/ር አል ማርያም ጋር ንግግር ያደርጋሉ።
Nov 30: Nuremberg : Public meeting and fundraising
Dec 02: Frankfurt: Appearance at a rally; Meet with invited guests for dinner
Dec 05: Geneva: appearance at a rally
Dec 07: Amsterdam: Public meeting
Washington DC Public Meeting with Semayawi Party Chairman Eng. Yilkal Getnet – Sunday Dec 15, 2013 – Sheraton Arlington Hotel.     Source Ethiopian media forum 
Blue-Party-at-USA1

የህዝባችን መከራ የወያኔ የፖለቲካ መጠቀሚያ አይሆንም! (ግንቦት 7)



Ginbot 7 weekly editorialበሳውዲ አረቢያ ውስጥ እጅግ ብዙ ኢትዮጵያውያን አሁንም መከራና ስቃይ ላይ ናቸው። የደረጃ ጉዳይ ነው እንጂ ችግሩ በመካከለኛው ምስራቅ ሀገሮች በሚኖሩ ወገኖቻችን ላይ የተንሰራፋ ነው። በመላው አለም ተበትኖ የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ካለማቋረጥ ያደረገው ወገንና ሀገር አኩሪ ጩኸትና አቤቱታ ችግሩ በአለም ዙሪያ ትኩረት እንዲያገኝ ባያደረግ ኖሮ የወገኖቻችን መከራ ከዚህም በከፋ መልክ ይቀጥል እንደነበር ጥርጥር የለውም። አንድ ቀን እንኳን ለሚገዛው ህዝብ ሀላፊነትና ተጠያቂነት ተሰምቶት የማያውቀው የወያኔ ጉጅሌ መንግስት እግሩን እየጎተተ ቢሆንም ወደ ችግሩ አቅጣጫ እንዲመለከት የተገደደው በዚሁ የወገን ጩኸት መሆኑ ግልጽ ነው።
ወያኔ ስላልቻለ ነው እንጂ ይህንን ከአለም አጽናፍ እስከ አለም አጽናፍ ያስተጋባ የወገን ደራሽ ድምጻችንን አዲስ አበባ ላይ እንደ አደረገው በሃይል ለማፈን ወደኋላ አይልም ነበር።
ሀፍረት የለሾቹ የወያኔ መንግስት ባለስልጣኖች ይህን የተጋለጠ ሀገርና ህዝብ አዋራጅ ተግባራቸውን እና በውሸት የተበከለ ገመናቸውን ለመሸፈን ከዚያም አልፈው የዋሆችን በማታለል የፖለቲካ ትርፍ ለማትረፍ የተለመደ ቲያትር መስራቱን ተያይዘውታል። ቴዎድሮስ አድሃኖም ችግሩ ባለበት በሳውዲ መሬት ላይ ሳይሆን የሳውዲ አረቢያ መንግስት በራሱ ወጪ አሳፍሮ ቦሌ አውሮፕላን ጣቢያ ባፈሰሳቸው ኢትዮጵያውያን መሃል እየተጎማለለ ያዛኝ ቅቤ አንጓች ቲያትሩን ሲሰራ ትንሽ እንኳን ሀፍረት አይታይበትም።
እነዚሁኑ ወደ ሀገር የተመለሱ አእምሯቸው በችግር የተመሰቃቀለ ዜጎች ወደ ካሜራ እየገፉ ስለ ሳውዲ ኤምባሲያቸውና ስለመንግስታቸው ‘ድንቅ” አገልግሎት እንዲናገሩ ያስጠኗቸውን ተመሳሳይ አረፍተ ነገር መስማት የሚያሳዝን ባይሆን ኖሮ ተወዳዳሪ የሌለው ኮሜዲ ይወጣው ነበር።Dr. Tedros Adhanom Ghebreyesus, the Minister of Foreign Affairs of Ethiopia.
እውነቱ ዛሬ በሀገራችን የሰፈነው ስደትና አብሮት የሚመጣው መከራ ሁሉ ዋናው አምራች ፋብሪካ ወያኔ መሆኑ ነው። ወያኔ የገነባው ጥቂት ጀሌዎቹንና ሎሌዎችን ተጠቃሚ ያደረገና አብዛኛው ኢትዮጵያዊ በተለይ ወጣቱ በሀገሩ ተስፋ እንዲቆርጥ ያደረገው ስርአት ነው። የስደታችንና የመከራችን ምንጭ ስደት የሚመጣው በሀገር ተስፋ መቁረጥ ነው። እንጀራ ፍለጋና ጭቆናና አፈና ሽሽት አምልጠን በየባዕድ ሀገሩ እንድንከራተት የሚያደርገን የወያኔ ስርአት ነው። በታሪካችን ውስጥ ተሰደን በባዕድ የተዋረድነው በወያኔ ምክንያት ነው።
በሀገር ውስጥ በአፈና ስር ሆናችሁ፣ በውጪው አለምም በየኢምባሲው የምታሰሙት ጩኸትና የምታፈሱት እምባ እብሪትና ትእቢት ያደነደነውን፣ ዝርፊያ ያደነዘዘውን የወያኔን ልብ እንደማያሸብረው ማወቅ አለብን።
የወያኔ ሹማምንቶች ይግረማችሁ ብለው ከአላንዳች ሀፍረት ያውም በሳውዲ አረቢያ ወጪ ተጓጉዘው ሀገር የገቡትን ግራ የተጋቡ ስደተኞች ለፖለቲካቸው ማሳመሪያ በቴሌቪዥን ስእልና ፎቶግራፍ መነሻ ሲያደርጉትና ለፖለቲካ ስራ መሳሪያ ሲያውሉት እያየን ነው። በነሱ ቤት ብልጥ ፖለቲከኞች መሆናቸው ይሆናል። በኛ ቁስል ላይ እንጨት እየሰደዱ መሆናቸውን ግን ፈጽሞ አይሰማቸውም።
ወያኔ በመካከለኛው ምስራቅ ተሰደው ለፍተው የሚኖሩት ወገኖቻችን በምን ሁኔታ ላይ እንዳሉ ያውቃል። ቢያንስ በየኢምባሲው ያስቀመጣቸው ነጋዴዎች ይነግሩታል። ችግሩን እንዳላየና እንዳልሰማ የሚያየው ከዜጎች ይልቅ እነሱ አፈር ግጠው ለፍተው ለሚያመጧት የውጪ ምንዛሬ የበለጠ ፍቅር ስላለው ነው። በዚህ ተግባሩ ወያኔ ወገኑን የሸጠ ባሪያ ፈንጋይ ነጋዴ እንጂ የመንግስት መሪ መሆኑ ያጠራጥራል።
ግንቦት 7 የፍትህና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ዘወትር እንደሚለው ሁሉ ይህ የዜግነትና የሀገር ውርደት፣ ይህ ሁሉ የወገን መከራ የሚቆመው የዚህ ሁሉ መሰረት የሆነው ወያኔና ስርአቱ ከመሰረቱ ሲነቀልና ሲወገድ መሆኑን ላፍታም አይዘነጋውም።
እንባችን የሚደርቀው ደማችን በየቦታው መፍሰሱ የሚቆመው መብታችን እንደዜጋ ተከብሮ ቀና ብለን የምንሄድበት ሀገር በትግላችን የተቀዳጀን ጊዜ ብቻ ነው።
ግንቦት 7ን ተቀላቀሉ በያላችሁበት ግንቦት 7 ሁኑ!! እኛ ከዚህ ውርደት ሞቶ የሚገኘው ነጻነት ይሻላል ብለን የተነሳን ልጆቻችሁ ነን። እርሰዎስ?
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

Thursday, November 28, 2013

ረዳት ፕሮፌሰር ግዛቸው ሽፈራው መጻፋቸውን አስመረቁ


በዳዊት ሰለሞን

በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቴክኖሎጂ ዲፓርትመንት የኬሚካል ፕሮሰስ ኢንዳስትሪን ለሰላሳ አመታት በማስተማር በመስኩ ከፍተኛ እውቅናን ያተረፉት ረዳት ፕሮፌሰር ግዛቸው ሽፈራው ‹‹the process technology of chemical and allied industries"በማለት የሰየሙትን ቅጽ አንድ የመማሪያና ማስተማሪያ መጽሐፍ በዩኒቨርስቲው በተዘጋጀ ደማቅ ስነ ስርዓት በማስመረቅ አበርክተዋል፡፡

500 ገጾችን የያዘው ጥልቅ ምርምር የተደረገበት መጽሐፍ በኢትዩጵያዊ ባለሞያ ተዘጋጅቶ መቅረቡ የመጀመሪያው በመሆኑም ግዛቸው ከሞያ አጋሮቻቸው አድናቆትን አትርፈውበታል፡፡
ከለንደን ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ማስተርሳቸውን የሰሩት ምሁሩ ከጋናው ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ በኬሚካል ኢንጂነሪንግ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል፡፡የጋናውን ዩኒቨርስቲ ከመቀላቀላቸው ቀደም ብሎ ከባህር ዳር ዩኒቨርስቲ የሶስተኛ ዓመት የመካኒካል ኢንጂነሪንግ ተማሪ ነበሩ፡፡
በተለያዩ አለም አቀፍና በአገር ውስጥ በሚገኙ ተቋማት በመስራት ለአገራቸው እውቀታቸውን ያበረከቱት ረዳት ፕሮፌሰሩ በኢትዩጵያ እውነተኛ የሆነ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ይገነባ ዘንድ በሰላማዊ መንገድ በመደራጀት ያመኑበትን በአደባባይ በመግለጽ ይታወቃሉ፡፡
በአሁኑ ወቅት የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቤት አባል የሆኑት ግዛቸው ፓርቲውን ለመጪዎቹ አራት አመታት ለመምራት ራሳቸውን በዕጩነት ማቅረባቸው ይታወቃል፡

Wednesday, November 27, 2013

የልጆች አስተዳደግ እና የቤተሰብ ውይይት ሴሚናር (Family communication Seminar) በሰላም የኢትዮጵያ ሴቶች ማህበር በኖርዌ የተዘጋጀ

ኖቨምበር 16,11.2013 የልጆች አስተዳደግ እና   የቤተሰብ ውይይት  ሴሚናር (Family communication and barneoppdragelse Seminar))   ሰላም የኢትዮጵያ ሴቶች ማህበር  በኖርዌ አዘጋጅነት  የተለያዩ ባለሞያዎችን በመጋበዝ ህብረተሰቡ ግንዛቤ እንዲኖረው አድርጓል በማድረግም ላይ ይገኛል ። ስለዚህ  በእለቱ ተገኝቺ ዝግጅቱን በመቅረጽ በፕሮግራሙ ላይ በተለያየ ምክንያት ላልተገኛችሁ ወግኖቻችን እንዲደርስ በማለት ልኬዋለሁ ሙሉውን ዝግጅት ከቪድዮ  ይመልከቱ ሶስት
 ክፍል ስላለው ሳይሰለቹ ይመልከቱት በጣም ጠቃሚና አስተማሪ ስለሁነ እንዳያመልችሁ  በማለት ምክሬን አስተላልፋለሁ። መልካም ጊዜ  ቸር ያሰማን 

እስክንድር አሰፋ
                                     
                            part one    
                    part two


                     part Three
                                          

Monday, November 25, 2013

Police harassed and detained runners at the Great Ethiopian Run in Addis Ababa



Woyanne’s federal police has harassed and detained runners at the Great Ethiopian Run on Sunday, Nov. 24, for speaking out against the mistreatment of Ethiopians in Saudi Arabia.


Monday, November 18, 2013

BBC: Ethiopians demonstrate outside Saudi embassy in London

There's been growing anger among Ethiopians in and outside the country, 
about the way that some of their compatriots have been treated in Saudi Arabia.
Things came to a head following an ultimatum for illegal migrant workers to leave the country.
And there were clashes in Riyadh which led to several deaths last week.
On Monday, there have been demonstrations at Saudi embassies around the world.
BBC Africa's Kasim Kayira went to the one in London.

Source: bbc.co.uk/news/world-africa-24994854


Saturday, November 16, 2013

Crazy Photos Are Coming Out Of Saudi Arabia After Rain Leaves Capital Flooded Read more: http://www.businessinsider.com/ridayh-rain-floods-city-2013-11#ixzz2krEC7jrJ

Riyadh, the 5 million strong capital of Saudi Arabia, generally doesn't receive much rainfall over the year. One source says that, on average, just 0.2 inches of rain fall in November.
It's perhaps because of this that the city has been unable to handle around two hours of heavy rain today. Residents are in shock, with many Internet users are posting pictures of flooded streets.


Read more: http://www.businessinsider.com/ridayh-rain-floods-city-2013-11#ixzz2krESLFzf



View image on Twitter

Here are some images that appear to show the flooding:
View image on Twitter

View image on Twitter

View image on Twitter

View image on Twitter

Riyadh is now like the sea due to rain
View image on Twitter

View image on Twitter

Friday, November 15, 2013

Ethiopian police brutally beat, arrest demonstrators at the Saudi Embassy (Text+Video)

በሳውዲ ኢምባሲ የተጠራው የተቃውሞ ሰልፍ በፖሊስ ተበተነ፤ ከቀናት በፊት ከሳውዲ የተመለሰች ወጣት በሰልፉ ድብደባ ደርሶባታል
15 የፓርቲው አመራሮች ታስረዋል
አውራምባ ታይምስ (አዲስ አበባ) – በቅርቡ የሳውዲ አረቢያ መንግስት በንጹሀን ኢትዮጵያዊያን ላይ የፈጸመውን ኢ-ሰብአዊና እንስሳዊና ድርጊት በመቃወም ሰማያዊ ፓርቲ የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ፤ ፖሊስ በወሰደው የኃይል እርምጃ ተበተነ፡፡
ዛሬ አርብ፣ ህዳር 6 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ 5፡00 ሰዓት በተለምዶ ወሎ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው ስፍራ ከአይቤክስ ሆቴል ፊለፊት በሚገኘው የሳውዲ አረቢያ ኢምባሲ ደጃፍ የተጠራው ሰላማዊ ሰልፍ የፓርቲው አባላትና አመራሮች እንዲሁም ጋዜጠኞችና ከቀናት በፊት ከሳውዲ አረቢያ የተመለሱ ዜጎች የተሳተፉበት ነበር፡፡ ሆኖም ሰልፉ ለጥቂት ደቂቃዎች ከተካሄደ በኋላ ፖሊስ ሰልፈኞቹን ለመበተን በወሰደው የሃይል እርምጃ በተወሰኑ ሰልፈኞች ላይ የአካል ጉዳት ደርሷል፡፡ በስፍራው የተገኘው የአውራምባ ታይምስ ዘጋቢም የፖሊስ ዱላ ከመቅምስ አላመለጠም፡፡demo
ፖሊስ ክፉኛ ከደበደባቸው ሰልፈኞች መካከል በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ድጋፍ ባለፈው ረቡዕ ወደ አገራቸው የተመለሱ ዜጎች ይገኙበታል፡፡ ከትናንት በስቲያ ወደ አገሯ መመለሷን ለአውራምባ ታይምስ የገለጸች አንድ ወጣት እንደገለጸችው ‹‹ሌሎች ያደረሱብ በደል አንሶ፤ በራሳችን ወገን በገዛ አገራችን እንዴት እንዲህ አይነት ድብደባ ይፈጸምብናል›› ብላለች፡፡
ሌላው ከሳውዲ የተመለሰ አንድ አስተያየት ሰጪ በበኩሉ ‹‹እንኳን እዚህ እዛም የጭካኔ እርምጃቸውን ተቋቁመን በድፍረት ሰልፍ አካሂደናል፤ በአገራችን እንዴት ሰልፍ እንከላከላለን›› ሲል በግርምት ተናግሯል፡፡
ለአውራምባ ታይምስ ዘግይቶ በደረሰ መረጃ መሰረት የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር የሆኑት ኢ/ር ይልቃል ጌትነትን ጨምሮ 15 አመራሮችና አባላት ከሰልፉ ጋር በተያያዘ ለእስር ተዳርገዋል፡፡
በጉዳዩ ላይ አስተያየት እንዲሰጡ ጥያቄ ያቀረብንላቸው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ም/ኃላፊ አቶ ሽመልስ ከማል ሰልፉ ፍቃድ ያልተሰጠው ህገወጥ ሰልፍ ነው ካሉ በኋላ ስለ ሰላማዊ ሰልፍ በተደነገገው አዋጅ ላይ ማንኛውም ሰልፍ ከእምነት ተቋማትና ኢምባሲዎች በ500 ሜትር ርቀት ላይ መካሄድ አለበት የሚለውን የአዋጁ ክፍል በመጣስ ህዝብና ህዝብ ሊያጋጩ የሚችሉ የጸረ-አረብ ስሜት የሚንጸባረቅባቸው ዘረኛ መፈክሮች በዚህ ህገወጥ ሰልፍ ሲስተጋቡ ፖሊስ ዝም ማለት አልነበረበትም፡፡ እርምጃውም ተገቢ ነበር ብለዋል፡፡
የፋሺሽት መፈክር አንግቦ በተጎሳቆሉ ዜጎች ስም የፖሊቲካ ትርፍ ለማግኘት መጣር ብሎም መንግስት በዜጎቹ ግዴለሽ እንደሆነ አስመስሎ ማቅረብ ኃላፊነት ይሰማኛል ከሚል የፖሊቲካ ድርጅት አይጠበቅም፤ ያሉት አቶ ሽመልስ ‹‹የሳውዲ መንግስት በአገሩ የአሰሪና ሰራተኛ ህግ መሰረት እርምጃ የመውሰድ ሉአላዊ መብት እንዳለው እንገነዘባለን፤ እኛ ደግሞ የሚመለሱ ዜጎቻችንን በአገራቸው አምራችና ስራ ፈጣሪ እንዲሆኑ በዘላቂነት ለማቋቋም በአገር ደረጃ ብሄራዊ ኮሚቴ አዋቅረን ስራ እየሰራን ነው፡፡›› ብለዋል


TPLF security attacks peaceful protesters at the Saudi Arabia embassy in Addis Ababa, Ethiopia


Today around 5:15 AM Ethiopia local time few protesters were out on the streets and we have witnessed federal police were attacking them. Among them there were old people. What’s even more heart breaking was the Saudi Embassy people were sitting on their roof tops and smiling when the TPLF federal police beat up their own people. The idea of coming together today was not about the current government. It’s about our people who are being brutalized in Saudi Arabia.

ዛሬ ማምሻውን ወያኔ እንደለመደው ያው "ሰልፉ ሌላ አላማ ነበረው!!" ብሎ ይወነጅላል በሽመልስ ከማል አንደበት:: ፖሊስ አሁንም ህዝቡን በማስፈራራት ላይ ነው ::ወሎ ሰፈር በሚገኘው ሳኡድኣረቢያ ኤምባሲ የተቃውሞ ድምጾች ለማሰማት የወጡ ዜጎች በፖሊስ ተደብድበዋል:: በርካቶች ታስረዋል:: ሰልፉም በፖሊስ ቆመጥ እና አላስፈላጊ እርምጃ ተበትኗል::


Image

Image

Image

Image

Image

Image

Image

Image

Thursday, November 14, 2013

Protest at Saudi Arabia embassy Tamagne Beyene Nov 14,11.2013



አንድ አንዳርጋቸውን መግደል የነፃነቱን ትግል ማስቆም አይቻልም


የጠቅላይ ሚኒስትሩ ብሔራዊ ደህንነት አማካሪ የጠቅላይ ሚንስትሩን ቢሮ በርግዶ ገባ። ግንቦት ሰባትን በተመለከተ እቅዳችንን ልነግርህ ነው የመጣሁት ሲል ነገሩን ጀመረ።

እሺ ምንድ ነው እቅዱ ?

የአንዳርጋቸውን፤ ጓደኞቹንና አንዳንድ የኤርትራ ባለስልጣኖችን ለመግደል ዝግጅቱ ተጠናቋል። ኤርትራ ድረስ ሂዶ “መስዋዕትነት” ለመክፈል የሚችል አንድ ሰው አግኝተን ልከናል። ግዳጁን ፈፅሞ ሲመጣ አንዳንድ ነገሮች እናደርግለታል። እርሱም ተስማምቷል።ጥቅምት 28 የምስራች እንሰማለን። እስከዛው ግን ፍተሻዎች እንዲጠናከሩ ወጥተህ ተናገር።

ሰውየው “already” ተልኳል ማለት ነው ?

አዎን ከተላከ አምስት ወር ሁኖታል።

የሚሳካ ይምስላችኋል ?

አዎን . . በሚገባ! እኛ ሞክረነዉ ያልተሳካ ምን ነገር አለ? . . . ጌታዬ። በደንብ ነው የሚሳካው። ዛሬ እዚህ መጥቼ የማሳስብዎት ይህ ጉዳይ ሲታቀድም ሲፈጸምም አልሰማሁም ብለዉ እንደ እግር ኳሱ እንዳያሳፍሩን ብዬ ነዉ።

አይዟችሁ እናንተም አታሳፍሩኝም እኔም አላሳፍራችሁም። እሺ ሰምቼያለሁ። አለ “አማኝ ነኝ ባዩ” ደሳለኝ ኃ/ማሪያም ምንም ዓይነት ወንጀል ያልሰሩ የአገሪቷ ምርጥ ልጆች ደማቸው በከንቱ እንዲፈስ እየተስማማ።

“ድሃ በህልሙ ቅቤ ባይጠጣ ንጣት በገደለው “ሲሉ አመሳጠሩ የሃገራችን ሰዎች።

“ቀፎው ነው እንጂ ሲም ካርዱ ከእኛ ነው” የተባለለትና እና በነፍሰ ገዳዮቹ ወንበር የተቀመጠውን የደሳለኝ ኃ/ማሪያምን ጉዳይ በዚህ እናበቃለን።

ህወሃቶች የንጹሃን ዜጎችን ደም በከንቱ ሲያፈሱ የኖሩ ነብሰ ገዳዮች እንደሆኑ የሚታወቅ ነው። አሁንም ክብሬንና ነፃነቴን የሚሉ ዜጎችን ይዘው ደብዛቸውን ለማጥፋት ብዙ ዓይንና ብዙ ጆሮዎችን በየቦታው አቁመናል እያሉ ያቅራራሉ። ይሄን ሁሉ ዓይንና ጆሮ ይዘንስ የሚያሸንፈን ማን ነው ? ሲሉም ይደመጣሉ። እነርሱ እንደሚሉት ዓይኖቻቸው ማየት፤ጆሮዎቻቸውም መስማት የሚችሉ አይደሉም። የህወሃት ዓይኖች ማየት የተሳናቸው እውራን፤ ጆሮዎቻቸውም ማድመጥ የማያውቁ ደናቁርት እንደሆኑ የታወቀ ነው። ህወሃቶች ይህን የማይሰማ ጆሮና ፤ማየት የተሳነውን ዓይን ይዘው እየተደናበሩ፤ ይህን ለመደበቅ ህይዎት ያላቸው መስለው ይታያሉ። አዎን ህወሃቶች ጭው ባለ በርሃ ላይ ብቻችሁን እንደቆማችሁ እወቁ። የሚነገረው እና የሚሆነው በሙሉ ስለተሰወረባችሁ በብዙ ሚሊየኖች መሃከል ብቻችሁን እርቃናችሁን ቀርታችኋል። ብዙ ሚሊዮን ዓይኖች እና ጆሮዎች በእናንተ ላይ መተከላቸውን ልናስታውሳችሁ እንወዳለን።

ግንቦት ሰባት የፍትህ፤የነፃነት እና የእኩልነት ንቅናቄ እንደ ህወሃት-ኢህአዴግ ጆሮዉ የተደፈነና አይኑ የታወረ ድርጅት አይደለም። ግንቦት ሰባት ንቅናቄ የሚያይ ዓይን፤ የሚሰማ ጆሮና የሚያስተዉል ልቦና ያለው ህያው ንቅናቄ ነው። የግንቦት ሰባት ንቅናቄ ጥያቄ ግልፅ ነው። ነፃነት ! ፍትህ ! እና ዲሞክራሲ ! ናቸው። እነዚህ ጥያቄዎች በአግባቡ መልስ እንዲያገኙ የሚከፈለውን መስዋዕትነት ለመክፈል ተነስተናል ጉዞ ጀምረናል፤ ሺ አንድአርጋቸውን ፈጥረናል። ልብ ይበሉ ነፃነት ፍትህ እና ዴሞክራሲ ለሰው ልጆች የተሰጡ ክቡር ስጦታዎች ናቸው። ህወሃት እነዚህን ክቡር ስጦታዎች ከዜጎች ላይ ነጥቆና ህዝብን ረግጦ መቀጠል የለበትም። ህወሃት የዜጎችን ነፃነት ነጥቆ ፤ ፍትህን አጓድሎና ህዝብን ረግጦ እንደከዚህ በፊቱ በሠላም እኖራለሁ ብሎ የሚያስብ ከሆነ ተሳስቷል። በህወሃት ቅዥት አገራችን ተጎድታለች። ህዝቧም ለማያባራ ጉስቁልናና ውርደት ተዳርጓል። ብዙዎችም አገር አልባ ሁነው በየሰው አገሩ መፃተኛ ሁነው እንዲኖሩ ተገደዋል። በእኛ እምነት በአገራችን ላይ እየደረሰ ላለው ውርደት በዋናነት ተጠያቂው ህወሃት ነው። ህወሃት የኢትዮጵያ ዋነኛው ጠላት ነው የምንለውም ዜጎቻችንን ለጉስቁልናና ለውርደት ስላደረገም ጭምር ነው። እኛ ይህን አገር በቀል ጠላት ከሥሩ ነቅለን ለመጣል ተነስተናል። ከዚህ ትግል የሚያቆመን ምንም ዓይነት ምዳራዊ ኃይል እንደሌለ ህወሃቶች እንዲያውቁት እንፈልጋለን። ህወሃቶች አንገታችንን አስደፍተው አይገዙንም። ጥቁር ደም ያፈራቻቸው የቁርጥ ቀን ውድ ልጆቿ የነጻነት ታሪክ በጥቁር ቀለም ይጻፍ ዘንድ የሚያደርጉትን ሀገርን የማዳን ጥሪ እንዲህ በቀላሉ መግታት ከቶ አይቻልም። ወያኔዎች አትደናበሩ! ጋሬጣውን መለየትን ለእኛ ተውሉን።

ታዲያ ይህን ንቅናቄ አንድ አንዳርጋቸውን በመግደል ማስቆም የሚቻል የሚመስለው ጅላ ጅል ቡድን አገሪቷን እየገዛ በመሆኑ ተቆጭተናል። አንዳርጋቸውን መግደል ሌሎች በርካታ ኢትዮጵያዊ አንዳርጋቸውን መፍጠርና ትግሉንም የሚያጠናክር እና የሚያፋፍም መሆኑን አልተረዱም። የኢትዮጵያ ህዝብ የእምቢተኝነት፣ የአልገዛም፣ የነጻነት ታሪክን ለማስከበር መሰዋእትነትን ለመክፈል ዝግጁ መሆንን ከአንዳርጋቸው ከተማረ ቆይቷል። መቆጨታችን ግን እንዲሁ በቁጭት ብቻ የሚቀር የሚመስለው ካለም ድግሞ ተሳስቷል። ይሄ ቁጭት በየደረሱበት የንፁሃንን ደም በከንቱ ማፍሰስ አገር መምራት የሚመስላቸውን ህውሃቶች ከተንጠለጠሉበት ዙፋን አውርደን በልካቸውና በአቅማቸው እንዲኖሩ ለማድረግ የጀመርነውን ትግል ይበልጥ አጠናክረን እንድንቀጥል ያደርገናል። ህወሃት ውስጥ እንደ ሰው ማሰብ የሚችል ግለሰብ ካለ አሁን ቆም ብሎ እንዲያስብ እናሳስበዋለን። ጀንበር ሳትጠፋባችሁ ለነጻነት፣ ለዲሞክራሲና ለፍትህ የሚደረገውን ትግል ተቀላቀሉ። እርግጥ ነው ለነፃነት የሚደረገው ትግል በየመስኩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና ህወሃትም የእጁን እንደሚያገኝ ምንም ዓይነት ብዥታ እንዳይኖራችሁ ልንነግራችሁ እንወዳለን።

ግንቦት ሰባት የቆመበት መሠረት ፅኑ፤ ዓላማውም ህዝባዊ ነው። በዚህ በፀና መሠረት ላይ ህዝባዊውን ዓላማ አንግበው የተነሱ ሚሊዮኖች አሉ። እነዚህ ሚሊየኖች የሌሉበት ሥፍራ የለም። ከቤተ-መንግስት እስከ እርሻ ማሳ፤ ከስለላ ተቋማት እስከ አገሪቷ መከላከያ ኃይል፤ ከሃይማኖት ተቋማት እስከ መንግስት መሥሪያ ቤቶች፤ ከዘመናዊ ትምህር ተቋማት እስከ ተከበሩ ገዳማት ድርስ ለክብራቸው ዘብ የቆሙ ሚሊየኖች አሉ። እነዚህ ሚሊኖች የቆሙት መረቅ የበዛበትን ወጥ ዓላማ አድርገው ሳይሆን በፀናው መሠረት ላይ ለተተከለው ክቡር ዓላማ ነው። ይህ ክቡር ዓላማ ነፃነት፤ ፍትህ ፤እኩልነት እና የህግ የበላይነት እንጂ ሌላ አይደለም። እነዚህ ሚሊየኖች አትኩረው ማየት የሚችሉ ድንቅ ዓይኖች ያሏቸው፤ አጥርተው ማድመጥ የሚችሉ ክቡራን ጆሮዎች ያሏቸው መሆናቸውን ህወሃቶች እንዲያውቁት እንወዳለን።

ግንቦት ሰባት ማንንም ፍርሃት እና ድንጋጤ ውስጥ መክተት አይፈልግም።እንዲያውም ግንቦት ሰባት ንቅናቄ የሚታገለው ዜጎች ሁሉ ከፍርሃት ነፃ ሁነው በደስታ እንዲኖሩ ለማስቻል ነው። ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን ካሁን ወዲያ ከግንቦት ሰባት ንቅናቄ ዓይንና ጆሮ የሚያመልጥ አንዳችም ነገር እንደማይኖር የሚያሳድደን ቡድን እንዲያውቀው እንፈልጋለን። ዓይንና ጆሯችን በሁሉም ሥፍራ በንቃትና በጥንቃቄ ነገሮችን እየተከታተሉ ይገኛሉ።

ህወሃቶች ከትዕቢታችሁ ብዛት የተነሳ የህዝቡን ምክር መናቃችሁን እናውቃለን።የወገኖቻችንንም ድምፅ ጫጫታ እያላችሁ እንደምትሳለቁም እናውቃለን። ይሄ እንደማይጠቅማችሁ ብዙ ግዜ ነግረናችኋል። የህዝቡን ምክር ስሙ፤ የወገኖቻችሁንም ድምፅ አድምጡ ብንላችሁ በእምቢታችሁ ፀንታችኋል። ልቦናችሁ እንደ ፈርዖን ልብ ደንድኗል።ልብ ማደንደን እንኳን እናንተን ለመሠለ ደካማ ፍጡር ይቅርና በዘመኑ እኔ “እምላክ” ነኝ እሰከ ማለት ለደረሰው ለፈርዖንም አልበጀም። እንዲህ ዓይነት የልብ ድንዛዜ እናንተ በዚያ ጠባብ ዓላማችሁ ጣልነው ለምትሉት ለመንግስቱ ኃ/ማሪያምም አልረባውም። አሁንም የእኛ ምክር አጭርና ግልፅ ነው። የመዘዛችሁትን የበቀል ሰይፍ ወደ ሰገባው መልሱ። የዘጋችሁትን በር ክፈቱ። የነጠቃችሁትን የዜጎች ነፃነት መልሱ። በህዝቡ ላይ ያወረዳችሁትን የፍርሃት ድባብ አስወግዱ። የተከላችሁትን የዘረኝነት እሾህ ንቀሉ። ከእውነት ጋርም ታረቁ። እንዲህ ብታደርጉ የዚያችን አገር በረከት ትበላላችሁ፤ እምቢ ብትሉ ግን የሚበላችሁን እሳት ማጥፋት አይቻላችሁም። መጥተናል!!

እኛም ከምን ግዜውም በላይ ተጠናክረናል። የትግል ዘርፋችን ሰፍቷል። በሁሉም አቅጣጫ መረባችን ተዘርግቷል። ከዚህ መረብ የትም አታመልጡም። ማምለጫ መንገዳችሁ አንድ ብቻ ነው። እርሱም የህዝቡን ድምፅ መስማት፤ እውነተኛ መልስ መስጠት እና ለህግ ተገዢ መሆን። አበቃን።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!!

Tuesday, November 12, 2013

በወያኔ የደህንነት መስሪያ ቤት የታቀደው የግንቦት 7 አመራሮች ላይ ያልተሳካው የመግደል ሙከራ ፈጻሚው በምስል

እስክንድር አሰፋ
12.11.2013
ኖርዌ
በወያኔ የደህነት መስሪያ ቤት የታቀደው በግንቦት 7 አመራሮች ላይ የመግደል ሙከራ  ሊፈጽም አስቦ ሳይሳካለት የቀረው ተስፈኛ ሙልቀን መስፍን  የታቀደለትን ሽልማት እንዳይሸለም ያኮላሹበት  ለሐገራቸው ሲሎ እራሳቸውን መስዋትነት አድርገው  በሰጡት የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች የግንቦት 7 ንቅናቄና ሕዝባዊ ሐይሎች በቁጥጥር ስር የዋለው  የሴሜን ጎንደሩ  ጉብል ። ፕሮግራሙን ESAT ቁልጭ አድርጎ ስለተረከው ከታች ያለውን link በመክፈት ልትከታተሉት ትችላላችሁ በመጨረሻ ለማስተላለፍ የምፈልገው ነገር ቢኖር በስልጣን ላይ ያላችሁም እንዲሁም ማንኛውም የወያኔ ደጋፊም ሆንክ አሽከር ወይም አገርህን ለከርስህ መሙያ ብለህ  ለወራሪ ጠላት አሳልፈህ በመስጠትህም በማፈራረስህም ከነአስተዳዳሪዎችህ  የታሪክ ተወቃሹችናተጠያቂዎች ስለሆናችሁ እራሳችሁን አጥፉ ወይንም በመጣችሁበት መንገድ ሐገራችንን ጥላችሁ ውልቅ በሉልን  ያለበለዚያ የምትፈሩትና የምትሸበሩለት ጀግናው ብሶት የወለደው የግንቦት ሰባት ጦር ውስጣችሁ ስለላለ  ብታስቡበት ይሻላል   ።
 ልብ ያለው ልብ ይበል !!!    
    

                                             ሙልቀን መስፍን
                            

http://ethsat.com/video/esat-special-program-o-millenium-nov-11-messay/

                   

                                 http://ethsat.com/video/esat-news-analysis-12-november-2013/
                               
                                 

                                 

ትግሉ መሯል፤ እኛም ዝግጁዎች ነን



በንቅናቄዓችን ፀሐፊ እና በግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል አመራር አባላት ላይ የተቃጣው ረዥም ጊዜ የወሰደ የግድያ ሴራ መክሸፉ አስደስቶናል። ይህ ሴራ የወያኔ የስለላና የግድያ ኃላፊዎች በሆኑት ጌታቸው አሰፋ እና ጸጋየ በርሄ የቅርብ ክትትል የተመራ፤ የአሻንጉሊቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ እውቅናና ይሁንታ የተሰጠው፤ ወያኔ ከፍ ያለ ተስፋ የጣለበት ሴራ ነበር።

“ወያኔ-ኦ-ሚሊኒየም” የተሰኘው ይህ በወያኔ የመጨረሻ ከፍተኛው አመራር የተመራው ሴራ ስለወያኔ ውስጣዊ አደረጃጀት ጠቃሚ መረጃዎችን ሰጥቶናል። ከዚህም በተጨማሪ የወያኔ ሹማምንት ስለ ኢትዮጵያ ሕዝብ ያላቸውን ንቀት፤ ከአመት በኋላ ስለሚደረገው ምርጫ ውጤት፤ ለሰላዮቻቸው ስለሚሰጡት ጉርሻ መጠን፤ እና ሌሎችም በርካታ ጉዳዮች ተስፋ ከጣሉበት ቅጥረኛ ነብሰ ገዳያቸው ጋር ካደረጉት የስልክ ንግግሮች ማድመጥ ይቻላል። ይህ ለበርካታ ጥናቶች በግብዓትነት ሊውል የሚችለውን በድምሩ ከስምንት ሰዓታት በላይ የሚፈጀው የስልክ ንግግር ቅጂ በሕዝባዊ ኃይሉ የመረጃ ክፍል አማካይነት ለሕዝብ በኢንተርኔት በነፃ ተለቋል። በአጋጣሚውም የወያኔ ገበና ተጋልጧል።
በአንፃሩ ደግሞ የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል የተደራጀው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ቢሆንም ምን ያህል ወያኔን እንቅልፍ እንደነሳ ተጨባጭ ማስረጃ ሆኗል። ይህ ለነፃነት ታጋዮች ከፍተኛ የስነልቦና ብርታት የሚሰጥ ነገር ሆኖ ተገኝቷል።
በእነዚህ ሁሉ ምክንያቶች የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል የተቃጣበትን ጥቃት ከማክሸፍ በተጨማሪ የወያኔን ገበና ማጋለጥ በመቻሉ የመጀመሪያው ሁነኛ ድል ተቀዳጅቷል።
ግንቦት 7 : የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ “ወያኔ ኦ ሚሊኒየም” አፕሬሽንን ላከሸፉ የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል አመራርና አባላት ያለውን አድናቆት ይገልፃል። ለወደፊቱም ተመሳሳይ ጥቃቶች ሊደርሱ የሚችሉ መሆኑን በመገንዘብ የመከላከል ብሎም የማጥቃት ኃይሉን እንዲያጠናክር ይመክራል።
የንቅናቀዓችን እና የሕዝባዊ ኃይሉ አመራርና አባላት ለመስዋዕትነት የተዘጋጁ ናቸው። “ወያኔ ኦ ሚሊኒየም” ተሳክቶ ቢሆን ኖሮ ትግላችን ይገታ ነበር ማለት አይደለም። ትግላችን መስዋዕትነትን የሚጠይቅ መሆኑን እናውቃለን። ጓዶች ሲወድቁ ሌሎች ሺዎች አርማቸውን አንስተው ትግሉን ይቀጥላሉ።
ትግሉ የሚጠይቀንን መስዋትነት ከፍለን ወያኔን ከሥልጣን አስወግደን ሕዝብ የሥልጣን ባለቤት የሆነባት ኢትዮጵያ እንደምትኖረን እርግጠኞች ነኝ።

ትግሉ መሯል፤ እኛም ዝግጁዎች ነን።

ድል ለግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል!!!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
ትግሉ መሯል፤ እኛም ዝግጁዎች ነን

በንቅናቄዓችን ፀሐፊ እና በግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል አመራር አባላት ላይ የተቃጣው ረዥም ጊዜ የወሰደ የግድያ ሴራ መክሸፉ አስደስቶናል። ይህ ሴራ የወያኔ የስለላና የግድያ ኃላፊዎች በሆኑት ጌታቸው አሰፋ እና ጸጋየ በርሄ የቅርብ ክትትል የተመራ፤ የአሻንጉሊቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ እውቅናና ይሁንታ የተሰጠው፤ ወያኔ ከፍ ያለ ተስፋ የጣለበት ሴራ ነበር።

“ወያኔ-ኦ-ሚሊኒየም” የተሰኘው ይህ በወያኔ የመጨረሻ ከፍተኛው አመራር የተመራው ሴራ ስለወያኔ ውስጣዊ አደረጃጀት ጠቃሚ መረጃዎችን ሰጥቶናል። ከዚህም በተጨማሪ የወያኔ ሹማምንት ስለ ኢትዮጵያ ሕዝብ ያላቸውን ንቀት፤ ከአመት በኋላ ስለሚደረገው ምርጫ ውጤት፤ ለሰላዮቻቸው ስለሚሰጡት ጉርሻ መጠን፤ እና ሌሎችም በርካታ ጉዳዮች ተስፋ ከጣሉበት ቅጥረኛ ነብሰ ገዳያቸው ጋር ካደረጉት የስልክ ንግግሮች ማድመጥ ይቻላል። ይህ ለበርካታ ጥናቶች በግብዓትነት ሊውል የሚችለውን በድምሩ ከስምንት ሰዓታት በላይ የሚፈጀው የስልክ ንግግር ቅጂ በሕዝባዊ ኃይሉ የመረጃ ክፍል አማካይነት ለሕዝብ በኢንተርኔት በነፃ ተለቋል። በአጋጣሚውም የወያኔ ገበና ተጋልጧል።
በአንፃሩ ደግሞ የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል የተደራጀው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ቢሆንም ምን ያህል ወያኔን እንቅልፍ እንደነሳ ተጨባጭ ማስረጃ ሆኗል። ይህ ለነፃነት ታጋዮች ከፍተኛ የስነልቦና ብርታት የሚሰጥ ነገር ሆኖ ተገኝቷል።
በእነዚህ ሁሉ ምክንያቶች የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል የተቃጣበትን ጥቃት ከማክሸፍ በተጨማሪ የወያኔን ገበና ማጋለጥ በመቻሉ የመጀመሪያው ሁነኛ ድል ተቀዳጅቷል።
ግንቦት 7 : የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ “ወያኔ ኦ ሚሊኒየም” አፕሬሽንን ላከሸፉ የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል አመራርና አባላት ያለውን አድናቆት ይገልፃል። ለወደፊቱም ተመሳሳይ ጥቃቶች ሊደርሱ የሚችሉ መሆኑን በመገንዘብ የመከላከል ብሎም የማጥቃት ኃይሉን እንዲያጠናክር ይመክራል።
የንቅናቀዓችን እና የሕዝባዊ ኃይሉ አመራርና አባላት ለመስዋዕትነት የተዘጋጁ ናቸው። “ወያኔ ኦ ሚሊኒየም” ተሳክቶ ቢሆን ኖሮ ትግላችን ይገታ ነበር ማለት አይደለም። ትግላችን መስዋዕትነትን የሚጠይቅ መሆኑን እናውቃለን። ጓዶች ሲወድቁ ሌሎች ሺዎች አርማቸውን አንስተው ትግሉን ይቀጥላሉ።
ትግሉ የሚጠይቀንን መስዋትነት ከፍለን ወያኔን ከሥልጣን አስወግደን ሕዝብ የሥልጣን ባለቤት የሆነባት ኢትዮጵያ እንደምትኖረን እርግጠኞች ነኝ።

ትግሉ መሯል፤ እኛም ዝግጁዎች ነን።

ድል ለግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል!!!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Monday, November 11, 2013

Shame on the Saudi government and people. This is what animals do, not human beings"

የወንድሞቻችንን ደም እያንዳንዱ የሳውዲ  ዝሪያ ይከፍላታል  ሰርቶ ባደረ ለፍቶ ጥሮ ግሮ በኖረ ይህ ነው ዋጋው? 
ግድ የለም ጊዜው ቢረዝምም አንቀርም እንዲህ እንደተዘረርን  ዋጋቸውን የሚከፍል አምላክ 
የእሳት ዝናብ ያዘንብባቸው አምላክ የሞቱትን ወንድሞቻችንን ነብስ ይማር 


                               https://www.youtube.com/watch?v=SfvyNtCS7UU

Assassinating popular leaders will only invigorate the people



On Thursday November 7, 2013; the Valiant Ginbot 7 Popular Force intelligence unit foiled the assassination plot that targeted the secretary of Ginbot 7: Movement for Justice, Freedom and democracy, and commanders and high ranked officers of Ginbot 7 Popular Force. This futile attempt by the coward TPLF regime that took place in Eritrea territory is yet another sign and proof that this blood-stained regime cannot and does not survive without spilling the blood of innocent Ethiopians. Ginbot 7 and the Ethiopian people at large are outraged by the TPLF regime’s recent assassination attempt, and they strongly denounce this shameful act that does not serve any purpose.
In the last twenty two years, the TPLF leaders assaulted or killed anyone who dare did anything to slightly oppose them, they hated one group of innocent people for no apparent reason, and they even managed to turn one of the most peaceful country in the world into a land of hate politics. All in all, genocide, hate, random killing, mass killing and now targeted killing – the TPLF regime has no shortage of reasons for guilt. Ginbot 7, Movement for Justice, Freedom and Democracy praises the heroic acts of the Ginbot 7 Popular Force in foiling the assassination attempt on its leaders and commanders, and uses this opportunity to pass a clear message to the arrogant TPLF leaders that Ginbot 7 Popular Force is part of the popular struggle that will never and can never be undermined by killing its leaders. In its attempt to perpetuate its power, the TPLF regime has gone to another inglorious dimension of targeted assassination of political leaders. Ginbot 7 wants to remind the TPLF regime and its killing squad that the shame and the sour defeat they were forced to swallow on Thursday November 7 is just the tip of the iceberg.
Once again, Ginbot 7 denounces the recent cowardly act of the Ethiopian regime in its strongest sense, and wants to remind the Ethiopian people that this is a wakeup call that must be answered with due diligence. Torturing and killing popular leaders has always been a worthless coward act that invigorates the people and creates more courageous leaders. We Ethiopians should cheerfully acknowledge that in its futile attempt to harm us, our enemy has wounded itself, now it’s up to us to hit the nail on the coffin.
We shall overcome!
Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy
Public Relation

Sunday, November 10, 2013

African workers in Riyadh seek repatriation after two riot deaths

(Reuters) - Thousands of mostly African workers gathered in Riyadh on Sunday seeking repatriation after two people were killed in overnight rioting that followed a visa crackdown by Saudi authorities.

One of those killed was a Saudi, said a government statement, and the other was not identified. An Ethiopian man was killed in a visa raid last week.

Ethiopia's foreign minister condemned the deaths, and told Reuters his government was working to bring its citizens home.

"This is unacceptable. We call on the Saudi government to investigate this issue seriously. We are also happy to take our citizens, who should be treated with dignity while they are there," Foreign Affairs Minister Tedros Adhanom said.

He said Addis Ababa had formally complained to Riyadh and that embassy staff were working to help Ethiopians return home.

Saudis abusing Ethiopian immigrants [Videos]




Hundreds of foreign workers clashed with police on Saturday night and into Sunday in Manfouha, a poor district of southern Riyadh where many low-income expatriates live.

Saudi authorities said 68 were also wounded, including 20 Saudis. More than 500 were detained and over 100 cars torched.

The Saudis said earlier this year they would no longer tolerate visa irregularities which have led to a large black market in cheap foreign labor in the world's top oil exporter.

Government raids on businesses, markets and homes began last week after a seven-month amnesty for foreigners to correct their visas or leave without paying penalties for overstaying or breaking other rules, ended on November 4.

CROWDED SCENES

In Manfouha, a long line of buses slowly filled up, as Africans arrived from neighboring streets, alone or in groups, and carrying bags. One man walked with his little daughter, while women carried babies, Reuters witnesses said.

Groups of people in Arab and south Asian dress stood on rooftops to watch. While the scene unfolded peacefully, many police stood nearby and several ambulances were also present.

"No iqama (residence permit)," said one man who said he was seeking repatriation to Ethiopia. He said he had arrived in Saudi Arabia illegally a year ago after paying smugglers 5,000 Saudi riyals ($1,333) to make the dangerous trip over the Strait of Hormuz and overland through Yemen.

"There's no money at home. Nothing at home," he said, pulling a suitcase on wheels.







በወያኔ የደህንነት መስሪያ ቤት የታቀደው የግንቦት 7 አመራሮች ላይና በሌሎች በኤርትራ በሚገኙት ተቃዋሚዎች ላይ ያልተሳካው የመግደል ሙከራ

  እውነተኛ መረጃዎችን  ለኢትዮጵያኑች በማቅረብ የታወቀው የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ጣቢያ(ESAT )ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ ባስተላለፈው ሰባር ዜና   የግንቦት 7 ንቅናቄ ዋና ጸሐፊ የሆኑትን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን  እንዲሁም የግንቦት 7 ሕዝባዊ  ሐይል  ባለ ስልጣናትን ለመግደል በታቀደው የወያኔ ኦ ሚሊኒየም ዘመቻ መክሸፉን ማቅረቡ ይታወሳል ዛሬ ከሞላ ጎደል ጋዜጠኛ ሴሳይ አጌና እና መሳይ መኮንን በእፍታ ዝግጅታቸው ለኛ በሚገባ ሁኔታ አቅርበውታል እንከታተለው።



                                 http://ethsat.com/video/esat-efeta-special-11-november-2013

Saturday, November 9, 2013

ኢትዮጵያውያን ሳዑዲ አረቢያ ኢምባሲ በመደወል በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰው ስቃይ እንዲቆም እንዲያሳስቡ አቀረበች

1394374_420880848034957_801329431_nበሳዑዲ አረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሰ ያለው ስቃይ እየበረታ ሄዷል። ዘ-ሐበሻ ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለችው ሲሆን በሳዑዲ የሚገኙ ወገኖቻችን በፌስቡክ መልዕክትና በስልክ እያደረሱን ካለው መልዕክት እንደተረዳነው “የወገናቸውን እርዳታ” ይሻሉ። በተለይ በሳዑዲ የሚገኙ ወገኖች እንደገለጹልን የሳዑዲ ዜጎች ኢትዮጵያውያኑን ከቤታቸው እያወጡ እየቀጠቀጡ ከመሆኑም በላይ ወደ አልታወቀ ስፍራ እየወሰዷቸው ነው። አስገድዶ መድፈሩ፣ ማሰቃቱ በርትቷል። እስካሁን በሳዑዲ ፖሊሶች እና ዜጎች እጅ ያልገቡት ኢትዮጵያውያንም ካሁን ካሁን እቤታችን ሰብረው ገቡ በሚል ስጋት ላይ ናቸው። በኢትዮጵያውያኑ ላይ የሚደርሰውን ጥቃትና የሰብአዊ መብት ጥሰት እንዲቆም ማንኛውም ወገን በያለበት ሃገር የሳዑዲ ኢምባሲ በመደወል እንዲጠይቅ፤ ብዙ ኢትዮጵያውያን በሚኖሩባቸው ሃገራት ደግሞ በየኢምባሲው ደጃፍ በመሄድ የተቃውሞ ሰልፍ በማድረግ የኢትዮጵያውያኑ ድምጽ እንዲሰማ ወገን እንዲተባበር ዘ-ሐበሻ ጥሪዋን ታስተላልፋለች።
በተለያዩ ሃገራት የሚገኙ የሳዑዲ አረቢያ ኢምባሲ ስልክ ቁጥሮች እና አድራሻዎች በጥቂቱ/ ከነዚህ ውስጥ ያልተካተቱ ሃገራት ኢምባሲዎች ካሉ በአካባቢዎ ካሉ የስልክ ማውጫዎች ወይም በጎግል አማካኝነት የኢምባሲውን ቁጥር ሊያገኙ ይችላሉ።


SAUDI ARABIAN EMBASSY IN WASHINGTON DC, UNITED STATES

Royal Embassy of Saudi Arabia in Washington, United States of America
601 New Hampshire Avenue, N.W.
Washington
20037
City: Washington DC
Phone: 0012023423800
Fax: 0012029443113
Website: http://www.mofa.gov.sa/SaudiMissionsAbroad/SaudiEmbassiesAbroad/Americas/Pages/EmbassyID40932.aspx
Email: usemb@mofa.gov.sa
Office Hours: 9 AM – 5 PM

SAUDI ARABIA EMBASSY IN LONDON, UNITED KINGDOM

30 Charles Street
W1J 5DZ
City: London
Phone: +44 (0)20 7917 3000
Fax: 00442079173113
Website: http://www.mofa.gov.sa/SaudiMissionsAbroad/SaudiEmbassiesAbroad/Europe/Pages/EmbassyID40923.aspx
Email: ukemb@mofa.gov.sa
Office Hours: 9 am – 4 pm except Friday until 3 pm

EMBASSY OF SAUDI ARABIA – BERNE SWITZERLAND

Address: Royal Embassy of Saudi Arabia Kirchenfeldstrasse 64 3005 Bern Phone Number: 00410313521555

SAUDI ARABIAN EMBASSY IN CANBERRA, AUSTRALIA

38 Guilfoyle Street
Yarralumla ACT, 2600
mailing address P.O. Box 9162 Deakin ACT 2600
City: Canberra
Phone: +61 (2) 62507000
Fax: 0262828911

SAUDI ARABIAN EMBASSY IN BRUSSELS, BELGIUM

Ambassade D`Arabia Sauodite Avenue Franklin Rosevelt, 45 1050
City: Brussels
Phone: 003226492044
Fax: 003226468538
Website: http://www.mofa.gov.sa/sites/mofaen/SaudiMissionsAbroad/SaudiEmbassiesAbroad/Europe/Pages/EmbassyID40911.aspx
Email: beemb@mofa.gov.sa
Office Hours: From 9 am – 3 p.m.


SAUDI ARABIAN EMBASSY IN OTTAWA, CANADA

The Royal Embassy of Saudi Arabia in Ottawa
201 Sussex Drive
K1 N1 K6 Ottawa
Ontario
City: Ottawa
Phone: (+1) 613-237 4100/ 001-613-2374101/ 001-613-2374102
Fax: 001-613-2370567
Website: http://www.mofa.gov.sa/sites/mofaen/SaudiMissionsAbroad/SaudiEmbassiesAbroad/Americas/Pages/EmbassyID40930.aspx
Email: caemb@mofa.gov.sa
Office Hours: 9am -4pm

SAUDI ARABIAN EMBASSY IN BEJING, CHINA

No. 1, Bei Xiao Jie, San Li Tun
100600
City: Bejing
Phone: 86-10-65324825 / 86-10-65325325
Fax: 86-10-65325324
Website: http://www.mofa.gov.sa/sites/mofaen/SaudiMissionsAbroad/SaudiEmbassiesAbroad/Asia/Pages/EmbassyID40942.aspx
Email: cnemb@mofa.gov.sa
Office Hours: From 8:30 a.m. to 4:30 p.m.

SAUDI ARABIAN EMBASSY IN ADDIS ABABA, ETHIOPIA

Gergos Area, 04 Qabali, House number B 179
1104 Addis Ababa
City: Addis Ababa
Phone: 251-11-4425643
Fax: 251-11-4425646
Website: http://www.embassy-saudi.com/ethiopia-addis-ababa.html
Email: etemb@mofa.gov.sa
Office Hours: From 9:00 am to 3:30 p.m.

SAUDI ARABIAN EMBASSY IN PARIS, FRANCE

5, avenue Hoche
75008
City: Paris
Phone: 0033146794000
Fax: 0033156794001
Website: http://www.mofa.gov.sa/sites/mofaen/SaudiMissionsAbroad/SaudiEmbassiesAbroad/Europe/Pages/EmbassyID40922.aspx
Email: fremb@mofa.gov.sa
Office Hours: From 9:00 a.m. to 4:00 p.m.

SAUDI ARABIAN EMBASSY IN THE HAGUE, NETHERLANDS

Alexander Street 19,
2514,JM
City: The Hague
Phone: +31-70-3614391
Fax: 0031703561452
Website: http://www.mofa.gov.sa/sites/mofaen/SaudiMissionsAbroad/SaudiEmbassiesAbroad/Europe/Pages/EmbassyID40925.aspx
Email: Saudiembassy@casema.nl
Office Hours: From 9:00 a.m. to 3:00 p.m.

EMBASSY OF SAUDI ARABIA – PRETORIA

Address: 711 Duncan St, Hatfild 0028 Phone Number: 0027123624230Phone Number 2: 0027123624231Phone Number 3: 0027123624233Fax Number: 0027123624239