ባለፈ ሳምንት አርብ ለቅዳሜ አዳር በፖሊስና በአወሊያ መስጊድ ዙሪያ በተሰባሰቡ የሙስሊም ማህበረስብ አባላት መካከል ግጭት ተቀስቅሶ ከመቶ በላይ ሲታሰሩ 17ሰዎች መቁሰላቸውን የኢትዮጵያ መንግስት ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።
የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ታሳሪዎቹ ወደ 500 እንደሚጠጉ ይገልጻል።
በዛሬውለት በጉዳዩ የጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት አቶ በረከት ስምዖን ያለፈቃድ የሚደረጉና “ህገ ወጥ” ያሏቸው መሰባሰቦች እንዲቆሙ ጥሪ አስተላልፈዋል። የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባል አቶ ካሚል ሸምሱን አነጋግረናል።