Saturday, July 14, 2012

ዘረኛውና አምባገነኑ መለስ ዜናዊ እራሱን ከሳተ ቦኋላ በቻርተር አውሮፕላን ወደ ቤልጂዬም ብራስልስ መወሰዱ ታወቀ

  • TPLF Business Empire

  • ዘረኛውና አምባገነኑ መለስ ዜናዊ እራሱን ከሳተ ቦኋላ በቻርተር አውሮፕላን ወደ ቤልጂዬም ብራስልስ መወሰዱ ታወቀ

    አገራችን ኢትዮጵያንና ህዝቧን በመጥላት ተወዳዳሪ የሌለው መለስ ዜናዊ ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ በተለከፈበት የካንሰር በሽታ ምክንያት አእምሮውን ከሳተ ቦኋላ ለአፋጣኝ የህክምና እርዳታ በቻርተር አውሮፕላን ወደ ቤልጂዬም ብራስልስ መወሰዱን የብራስልስ ምንጮቻችን ለዝግጅት ክፍላችን ገለጹ።
    እንደ ምንጮቻችን መረጃ ሞት አፋፍ ላይ ያለውን መለስ ዜናዊን የጫነው አውሮፕላን ከአዲስ አበባ የወጣው ረቡዕ ሌሊት ሲሆን ብራስልስ ሆስፒታል የገባው በማግስቱ ሃሙስ ጠዋት እንደሆነና አውሮፕላን ማረፊያ ሲጠባበቀው የነበረው አምቦላንስ ወዲያውኑ ተቀብሎት ዘወትር ወደሚታከምበት የሴንት ሉክ ሆስፒታል አድርሶታል።
    የግንቦት 7 ድምጽ የመለስ ዜናዊን መታመምና ለህክምና ወደብራስል ማቅናት ለመጀመሪያ ጊዜ የዘገበው ከ3 ወራት በፊት እንደፈረንጆች አቆጣጠር ባለፈው ሜይ ወር ውስጥ ሲሆን መረጃው ለህዝብ በተሰራጨ በሳምንት ጊዜ ውስጥ አሜሪካን አገር ተደርጎ በነበረው የ8ቱ ሃብታም አገሮች ስብሰባ ላይ ተገኝቶ ስለነበር ህመሙ ቀላልና በህክምና እርዳታ የሚፈወስ መስሎ ታይቶ እንደነበር ይታወሳል።
    በአፍቃሬ ወያኔና የጥቅም ተጋሪዎቹ ሥነልቦና ውስጥ በማንም ሃይል ሊደፈር የማይችል የጀግኖች ሁሉ አውራ አድርጎ የእራሱን ምስል ሲፈጥር የኖረው መለስ ዜናዊ በሰሜን አሜሪካው የጂ 8 ስብሰባ ላይ ጋዜጠኛ አበበ ገላው ባደረሰበት አንገት የሚያስደፋ ተቃውሞ በህዝብ ዘንድ መሳቂያ እና መሳለቂያ ሆኖ ለሁለት ወራት ከሰነበተ በኋላ በእርሱ መዋረድ የደነገጡት አድናቂዎቹ ከደረሰባቸው የሞራል ኪሳራ ሊያገግሙ የሚችሉበትን አንድም ኦፊሴላዊ ንግግር ሳያሰማ ዳግም ወደማይመለስበት ዘላለማዊ እንቅልፍ እየተጓዘ የመሆኑ አጋጣሚ ብዙዎችን አስገርሞዓል።
    ወያኔ ላለፉት 21 አመታት ሲፈጽማቸው የነበሩት ጸረ አገርና ጸረ ህዝብ ተግባሮች በሙሉ በዋናነት መለስ ዜናዊ የተመረዘበት የጥላቻና የበቀል ስሜት የወለዳቸው የበቀል እርምጃዎች እንደሆኑ በተለያዩ ምክንያቶች ከህወሃት የወጡ አንጋፋ የድርጅቱ አባላት በተደጋጋሚ ሲናገሩት የኖሩት ሃቅ ነው። በዚህም ምክንያት በህወሃት ውስጥ ያሉ የትግራይ ብሄርተኞች ከላይ ሆኖ ያሽከረክራቸው የነበረው የዚህ ሰው ከጫንካቸው ላይ መወገድ በሚፈጥርላቸው ዕድል ተጠቅመው ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ሂደት ለመፍጠር ተቃዋሚዎች እያደረጉ ያለውን ጥረት ሊደግፉና ከህዝብ ጋር የመታረቅ ዕድላቸውን እንደምርጫ 97 ሳያበላሹት እንዲጠቀሙበት አንዳንድ ለአመራሩ ቀረበታ ያላቸው ወገኖች ምክር መለገስ መጀመራቸው ይወራል።
    ለግንቦት 7 ድምጽ የደረሱ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት የመለስ ዜናዊ መጨረሻ በቀናት አለያም በወራት የተቆረጠ ሆኗል።

    2 comments:

    1. WHY ARE WE REJOICING ON SOMEONES PAIN?? WHY ARE WE REJOICING SOMEONES DEATH?,,,THATS NOT HUMANITY. ITS ONLY DEVIL WHO CAN REJOICE OVER PAIN AND DEATH OF PEOPLE. JESUS SAID " FORGIVE THEM FATHER WHAT THEY DON'T KNOW WHAT THEY ARE DOING" WE ALL SHOULD HAVE THAT LOVE TO FORGIVE WHO DID BAD TO US AND TO OUR PEOPLE. BROTHERS AND SISTERS LOVE YOUR ENEMY THATS HOW YOU DEFEAT YOUR ENEMEY. BUT IF YOU CARY HATE IN YOUR SELF AND WANT TO LEAD A NATION, THE ONLY THING YOU WILL DO THE PEOPLE IS PRACTICE HATE ,YOU MAY THINK YOU WONT DO THAT ITS BECAUSE YOU DONT KNOW HOW WICKED YOU HEART IS. SO PLEASE LET US NOT PLAY GAME. LET US ALL GATE IN TO LOVE AND EXERCISE LOVE THAT THE ONLY THING THAT BRINGS PEACE AND SECURITY.

      ReplyDelete
    2. PEOPLE LISTEN ,THIS IS HOW FAR OUR WICKEDNESS GOES,,CANT WE EVEN SHOW COMPASSION FOR HIS FAMILY ,HIS KIDS,,?,,IS THIS HOW ETHIOPIAN BEHAVE ?? THIS IS NOT GOING TO BRING PEACE NOTHING ,NOT EVEN YOUR STRUGGLE UNLESS WE LEARN TO LOVE OUR ENEMY.

      ReplyDelete