Saturday, May 11, 2013

ከሚ/ር መላኩ ፈንታ ጋር የታሠሩት 13 ተጠርጣሪዎች ዝርዝር


የፌዴራሉ የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፋንታ እንዲሁም ምክትላቸው አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስን ጨምሮ 13 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጉን ገለፀ፡፡
የኮሚሽኑ መግለጫ እንዳመለከተው ኮሚሽኑ ከህዝብ የተቀበላቸውን ጥቆማዎች መነሻ በማድረግ ከብሄራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎተ ጋር በመተባበር በጥናት ላይ ተመስርቶ ከቆየ በኃላ በተጠርጣሪዎች ላይ በቂ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን ማሰባሰብ ችሏል፡፡
ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት እስኪቀርብ ድርስ ተጠርጣሪዎቹ በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንዲቆዩ ማድረግም አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡
ከሁለቱ የመንግስት ባለስልጣናት ጋር በቁጥጥር ስር እንዲውሉ የተደረጉት ግለሰቦች
1.እሸቱ ወልደሰማያት – በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የአቃቤ ህግ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር
2.አስመላሽ ወልደማሪያም- የቃሊቲ ጉምሩክ ኃላፊ
3.ጥሩነህ በርታ- በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የተወረሱ ንብረቶች አስተዳደር ቡድን መሪ
4.አምኘ ታገለ- የናዝሬት ጉምሩክ ኃላፊ
5.ሙሉጌታ ጋሻው- በኦሮሚያ ልዩ ዞን መሀንዲስ
6.ከተማ ከበደ- የኬኬ ትሬዲንግ ባለቤት
7.ስማቸው ከበደ- የኢንተርኮንቴንታል ሆቴል ባለቤት
8.ምህረት አብ አብርሀ- ባለሀብት
9.ነጋ ገብረእግዚአብሄር- የነፃ ትሬዲግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ባለቤት
10.ዘሪሁን ዘውዴ -ትራንዚተርና ደላላ
11.ማርሸት ተስፉ – ትራንዚተርና ደላላ ናቸው፡፡
*********

No comments:

Post a Comment