Wednesday, January 2, 2013

የአረና ፓርቲ ጽህፈት ቤት በዶዘር ፈረሰ


ታህሳስ  ፳፪(ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም 


ኢሳት ዜና:-በሁመራ የሚገኘው የፓርቲው ጽህፈት ቤት በዶዘር እንዲፈርስ ከተደረገ በሁዋላ የድርጅቱ ጽህፈት ቤትም ተዘርፎአል። በተመሳሳይ መንገድም የድርጅቱ አባል የሆኑት የአቶ ገብረእግዚ ናዩ ቤት ያለምንም ማስጠንቀቂያ እንዲፈርስ ተደርጓል።
በተንቤን የድርጅቱ አባል የሆኑት አቶ ጸጋየም መታሰራቸው ታውቋል። በአቶ ገብሩ አስራት በሚመራው አረና ፓርቲ ላይ የትግራይ ክልል ባለስልጣናት የሚወስዱት እርምጃ እየከፋ መምጣቱን መዘገባችን ይታወሳል።

    No comments:

    Post a Comment