Tuesday, March 12, 2013

Members of Semayawi Party described the 'discrimination' as an Apartheid”-

ሃገራችን ኢትዮጵያ ከየት ወደየት እየተጓዘች ነው ?

Esconder  Asefa  12.03.2013 

እዮት ይህንን አሳፋሪና አሳዛኝ ትእይንት ወገኖቻችን በሃገራቸው ላይ በዲሞክራሲ መብታቸው ተጠቅመው የመናገርም ሆነ የመሰብሰብ  መብታቸውን ተጥሶ በሃገራቸው ላይ እንደ 7ተኛ ዜጋ ሲዋከቡና ሲራበሹ ማየት በጣም አሳፋሪ ነው ታዲያ ወገን ምን እስክንሆን ድረስ ነው የምንጠብቀው ? እኔ እንደማስበው አስር ድርጅት መስርቶ ሁልጊዜ መግለጫ ከማንበብ አንድ ሆኖ ዘር ፤ ሃይማኖት ፤ ብሄር ፤ ከመለየት በአንድነት ሆነን በአፓርታይድ አገዛዝ የተገዛውን ህዝባችንን እንድንደርስለት ያስፈልጋል ያለበለዚያ እንደ ቀበሌ እድር በየመንደሩ የእንትን ፓርቲ የእንትን ፓርቲ እያላቹ  የ3000አመት ባለታሪክ የሆነችውን ሃገራችን እንዳትፈራርስ እሰጋለሁ። ለዚህ ሁሉ በደል ተጠያቂ በስልጣን ላይ ያለው ዘረኛው መንግስት ብቻ አይደለም ምክንያቱም እንደ መልካም አስተዳደር  ከወያኔ መንግስት  ጋር በሰላማዊ ትግል ሃገራችንን ነጻ እናወጣለን ብለው ለእነሱ  መሳሪያ ሆነው ተቃዋሚ ድርጅቶች ነን እያሉ  በህዝብ ላይ የሚያሾፉትም ተጠያቂ  ናቸው። ወገን እንንቃ በተለይ በውጪ የምንኖረው ኢትዮጵያኖች እባካቹ  ባይሆን ድምጹ ለታፈነው ህዝባችን ድምጽ እንሁነው እኛ ተመችቶን እንደምንኖረው ሁሉ ወገኖቻችንም ይህንን ሰላም ይፈልጉታል የነሱ መሰቃየት ለኛም እንዲሰማን ያስፈልጋል ለወገን ደራሽ ወገን ነው ስለዚህ በአንድ መንፈስ በአንድ ሃይል መነሳት አለብን። 
ቸር ያሰማን  watch the video
ድል ለኢትዮጵያኖች 
ሞት ለከፋፋዮች
እስክንድር ከኖርዌይ 

h

Members of Semayawi Party/Blue Party had booked a dinner for last night at the Wabi Shebelle Hotel, Addis Abeba, to dine with Professor Mesfin and Dr. Yakob and have a round table talk about various issues. At the last minute, they were told “you can’t eat here”. One of those, who says had already paid 300 Et.B to eat his dinner, described the ‘discrimination’ as an “Apartheid”. Well, won’t complain here now myself, if find myself discriminated. Clip below shows some of the controversies…

No comments:

Post a Comment