Wednesday, July 31, 2013

የአዲስ አበባ ደህንነቶችና ፖሊሶች የአንድነት አባል ላይ ድብደባ ፈፀሙ

DSCN2379
የአንድነት ፓርቲ የአዲስ አበባ አመራር አባል የሆነው ወጣት ብርሃኑ ገረፋ ሐምሌ 22 ቀን 2005 ዓ.ም. ሳሪስ አካባቢ የፓርቲውን በራሪ ወረቀት ሲበትን በ1 ደህንነትና በ6 ፖሊሶች በህገወጥ መንገድ መታሰሩን ፓርቲው በተለይ ለፍኖተ ነፃነት አስታውቋል፡፡
ወጣት ብርሃኑ በደህንነት አባሉ በመሳሪያ ሰደፍ ጀርባውንና ጭንቅላቱን ከመመታቱ በተጨማሪ ፖሊሶችም እጁን ጠምዝዘው በቦክስ ግራ ጉንጩን መመታቱ ተጠቁሟል፡፡ በእስር ቤት ውስጥ አንድ ቀን አሳድረው ካንገላቱ በኋላ  ሐምሌ 23 ቀን 2005 ዓ.ም. በመታወቂያ ዋስ መለቀቁ ታውቋል፡፡
ወጣት ብርሃኑ የፀጥታ ኃይሎች ሲይዙት እጁን በካቴና እንደወንጀለኛ አስረው ሳሪስ አቦ አካባቢ በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ በእግር ከወሰዱት በኋላ ወደ አቃ ቃሊቲ ፖሊስ መመሪያ ወስደው ማሳደራቸው ታውቋል፡፡
- See more at: http://www.fnotenetsanet.com/?p=5151#sthash.kBSDKTiq.dpuf

Monday, July 29, 2013

10 Poorest Countries in The World (All in Africa)

You probably heard that Ethiopia has been a fast growing economy in the content recording very high growth rate not just in Africa but the world as well. Yet the new measurement known as the Multidimensional Poverty Index, or MPI, that will replace the Human Poverty index in the United Nations’ annual Human Development Report says that Ethiopia has the second highest percentage of people who are MPI poor in the world, with only the west African nation of Niger fairing worse. This comes as more international analysts have also began to question the accuracy of the Meles government’s double digit economic growth claims and similar disputed government statistics referred by institutions like the IMF.
  1. Niger
  2. Ethiopia
  3. Mali
  4. Burkina Faso
  5. Burundi
  6. Somalia
  7. Central African Republic
  8. Liberia
  9. Guinea
  10. Sierra Leone

What is the MPI?

People living in poverty are affected by more than just income. The Multidimensional Poverty Index (MPI) complements a traditional focus on income to reflect the deprivations that a poor person faces all at once with respect to education, health and living standard. It assesses poverty at the individual level, with poor persons being those who are multiply deprived, and the extent of their poverty being measured by the range of their deprivations.
The MPI can be used to create a vivid picture of people living in poverty, both across countries, regions and the world and within countries by ethnic group, urban/rural location, or other key household characteristics. It is the first international measure of its kind, and offers an essential complement to income poverty measures because it measures deprivations directly. The MPI can be used as an analytical tool to identify the most vulnerable people, show aspects in which they are deprived and help to reveal the interconnections among deprivations.

Why is the MPI useful?

According to the UNDP report, the MPI is a high resolution lens on poverty – it shows the nature of poverty better than income alone. Knowing not just who is poor but how they are poor is essential for effective human development programs and policies. This straightforward yet rigorous index allows governments and other policymakers to understand the various sources of poverty for a region, population group, or nation and target their human development plans accordingly. The index can also be used to show shifts in the composition of poverty over time so that progress, or the lack of it, can be monitored.
The MPI goes beyond previous international measures of poverty to:
  • Show all the deprivations that impact someone’s life at the same time – so it can inform a holistic response.
  • Identify the poorest people. Such information is vital to target people living in poverty so they benefit from key interventions.
  • Show which deprivations are most common in different regions and among different groups, so that resources can be allocated and policies designed to address their particular needs.
  • Reflect the results of effective policy interventions quickly. Because the MPI measures outcomes directly, it will immediately reflect changes such as school enrolment, whereas it can take time for this to affect income

Dr. Wondimu says Semhal Meles deposits $5 billion


የመለስ ዜናዊ የመጀመሪያ ልጅ ሰመሃል መለስ ኒው ዮርክ ውስጥ በሚገኝ አንድ ባንክ ውስጥ 5 ቢሊዮን ዶላር በ2011 ኣስገብታለች። ይህን ያሉት እንግሊዝ አገር እሚገኙት ምሁር እና የመንግስት ተቃዋሚ የሆኑት ዶክተር ወንድሙ መኮንን ናቸው። ዶክተር ወንድሙ የቼኩን ኮፒ አያይዘው ለእንግሊዝ ፓርላማ ሃውስ ኦፍ ኮመንስ አቅርበዋል። ሙሉውን እዚህ ያገኛሉ
July 26, 2013
Semehal Meles Zenawi, the daughter of the late Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi, has deposited $5 billion in one of the banks in New York, said Dr. Wondimu Mekonnen, an academic and opposition figure, during a recent presentation at the House of Commons in the U.K. The date on the cheque that Wondimu distributed states the money was lodged on October, 2011.
Wondimu also showed and distributed a copy of the cheque of the money she lodged to the members of the House who attended his presentation.
Celebrity Net Worth site said Meles Zenawi got a net worth of $3 billion. What a shame! That is wrong guys. Absolutely wrong.  I have got a copy of a cheque signed by Semhal Meles Zenawi, the daughter of Meles Zenawi himself, depositing in one of the New York banks $5 billion. I have got and I will give you the copy. Don’t ask me how it came into our possession but that is a fact.
Wondimu further said ”I think, Celebrity Net Worth, got it entirely all wrong. If that was the case, how come, a check in the name of his elder daughter Semhal Meles Zenawi, for US5 billion was deposited into a bank in New York? We will leave the investigation to Department of Fraud and Money Laundering Investigation of the United States”.

Sunday, July 28, 2013

Massive crackdown underway in Ethiopia

july 28, 2013
The Horn Times Newsletter July 28, 2013
by Getahune Bekele, South Africa

Massive crackdown underway on opposition stronghold of South Wollo, Ethiopia

It was a pre-dawn assault by hundreds of heavily armed federal police members backed by pro-TPLF local militia on the opposition UDJP strong hold of South Wollo province.
Massive crackdown underway on opposition in EthiopiaAccording to Finotenetsanet newspaper reporters, yesterday’s dawn- to- dusk raid targeted the twin towns of Haiq and Worebabu; and more heavy handed attacks are set to continue in other nearby towns and villages of the historic province.
Worebabu area UDJP leader Ato Edris Saed told Finotenetsanet that the police tried to disguise their act by telling people that they are looking for weapons.
Arage Hussein, UDJP’s financial officer in the town of Haiq said the police and the feared local militia searched the homes of all 16 members of UDJP leadership, each search lasting for up to two hours and more.
“I pleaded with the five police men and the militias who came to my home at dawn that I am a man of peace and never owned a firearm but they proceeded with the search and left empty-handed.” Ato Arage Added.
Moreover, according to South Wollo zone UDJP chairman Ato Bisrat Abi, the ruling party is on a campaign trail in the area, on a burgeoning run to discredit the UDJP leadership and its members. TPLF cadres have already organized anti UDJP meetings and demonstrations as part of the well planned crack down on dissenting voices in the region.
“Since the recent mass anti TPLF rallies organized in Dessie and Gonder cities, UDJP has been on the rise. The ruling junta’s cadres now have an implacable enemy right under their noses with the potential of bringing down the conjugal dictatorship. Therefore, I see it as normal for the authoritarian and corruption-ridden regime to wage an all-out war on the UDJP.” A respected political analyst who requested anonymity told the Horn Times from Addis Ababa.
Asked if UDJP has any chance of surviving the onslaught with no international support, with western powers still generously endowing the ruling minority junta; turning a blind eye on its undemocratic practices, the elderly analyst said it is up to the people of Ethiopia to rally around the party and its young and energetic leadership.
“Look, we all thought UDJP was hanging on life support system after the loss of its patriotic leaders in Andualem Arage and Natinael Mekonnen. Am astonished by how the current young leaders filled the leadership vacuum and make the party grow from strength to strength. I hope they will keep the momentum, keep the pressure on the junta and get serious violations and abuses such as this one in south Wollo quickly to the media. We are in better times today than yesterday.”

Arrests made after Friday’s protest rally in Addis Ababa

Posted by  on July 28, 2013


Tuesday, July 23, 2013

አገር እንደ ዳቦ


አገር እንደ ዳቦ

አገር እንደ ዳቦ እየተቆረሰ፣
ከሰላ ተበልቶ ጅቡቲ ደረሰ፣
ጅቡቲ ተበልቶ ኤርትራደረሰ፣
ኤርትራ ተበሌቶ ወልቃይት ደረሰ፣
በወልቃይት በኩል ጉምዝን ተሻግሮ ጋምቤላ ደረሰ፣
ለጎራሽ(ለጠላት) እንደያመች እየተገመሰ።
አገር እንደ ዳቦ እየተቆረሰ፣
ዳር ዳሩ ተበልቶ መሃል ተደረሰ።
ይህ ተላላኪ እንግዳ አስተናጋጅ እየተጣደፈ፣
ኢትዮጵያን ለማጥፋት
እየሸነሸነ አገር ለማስበላት፣
በክልል፣በጎሳ ቆራሽ አሰለፈ።

የውጭ ወራሪ ሌላ መንገድ ቢያጣ፣
አገሩን ለመያዝ(ለመግዛት) መለስ ብሎ መጣ።
ከሰሃራ በታች ከሱዳን ባሻገር፣
ከኬንያ ወዲህ በኢትዮጵያ ድንበር፣
መሬትና ቦታ መግዛት ካማራችሁ፣
እርካሽ ነጋዴ ኢህአድግ(ወያኔ) አለላችሁ።
ጣሊያንና እንግሊዝ ከአምሳ ዓመት በዃላ ከኢትዮጵያ በወጡ፣
ኢህአዳግን ፈጥረው እንደገና መጡ፣
በዲሞክራሲ ስም ከፋፍለው ሊግጡ።

በርካሽ ሸምተው በውድ ሊሸጡ፣
ያገር ውስጥ ነጋዴ መድረሻ ሊያሳጡ።
በስመ ፈላሻ፣በስመ ሎተሪ ሕዝብን እያሶጡ፣
መለስ ቀለስ ብለው ለመበተን መጡ።
ጥንትም ሰሜኑ ነው መግቢያና መውጫቸው፣
ወደ መሃል አገር መረማመጃቸው።

ኢራን፣ ሕንድ፣ ቻይና፣ ቱርክና እሩስያ፣
አውሮፓ አሜሪካ፣ሳውዲና ሉቢያ፣
በቅርጫው ገብተዋል በነጻው ገበያ፣
ወግድ ባይ በሌላት በኢትዮጵያ።
ያገሬ ደሃ ሕዝብ አትቀበላቸው፣
ከልማት ባሻገር ሌላ ግብ አላቸው።

ለውስጡ ተነፍጋ ለውጭ የቀረበች፣
እየተገመሰች፣እዬተቆረሰች፣
ኢትዮጵያ አገራችን ክብ ዳቦ ሆነች፣
በዚህ ከቀጠለ ሙልሙል ትሆናለች።
ያለም ነጋዳዎች ካለፈው ተማሩ፣
ሕዝብ ስልጣን ሲይዝ በባዶ እንዳትቀሩ፣
ከወያኔ ጋራ አትፈራረሙ አትደራደሩ፣
የሱ ብቻ አይደለም የዘጠና አምስት ሚሊዮን ሕዝብ ነው አገሩ።

Monday, July 22, 2013

የዩናይትድ ስቴትስ የስለላ ቅሌትና መዘዙ

 ስለ NSA የተለያዩ መፅሐፍት ያሳተመዉ ጋዜጠኛ ጀምስ ባምፎርድ እንደሚለዉ፥ እርስዎ ከዱባይ ወይ ከለንደን አዲስ አበባ ላለች ፍቅረኛዎ የፍቅር ኢሜል ይመይላሉ እንበል።ስኖዳን እና ብጤዎቻቸዉ ሐዋይ፥ ሜሪላንድ ወይም የፈለጉበት ቦታ ሆነዉ-ከፍቅረኛዎ እኩል ምናልባትም ቀድመዉ ኢሜልዎን ያነባሉ።ስልኩም---
Bildnummer: 51715405 Datum: 01.02.2007 Copyright: imago/INSADCO
Top Secret - Schriftzug auf einem Karteikartenreiter, Objekte; 2007, Symbolfoto, Studioaufnahme, Ordnung, geordnet, geordnete, sortiert, Sortierung, Katalogisierung, Karteikartenreiter, Register, Verwaltung, Akte, Akten, streng geheim, geheime Daten, Geheimnis, Geheimnisse, Betriebsgeheimnis; , quer, Kbdig, Gruppenbild, Deutschland, , o0 Behörden, Staat,, Personalakte; Aufnahmedatum geschätztየትንሹ ሠላይ ትልቅ ድፍረት፥ የትልቂቱ ሐገር ታላቅ ቅሌት።የልዕለ ሐያሊቱ ሐገር የሥለላ ቅሌት መነሻ፥አስተጋብኦቱ ማጣቀሻ፥ ያስከተለዉ ዉዝግብ መድረሻችን ነዉ-ላፍታ አብራችሁን ቆዩ።

የመረጃ ሰዎች ካንዱ መንግሥት ወደ ሌላዉ መኮብለል፥ ወይም መንግሥታት የተቀናቃኛቸዉን መንግሥት ሰላይ ማስኮብለል እንግዳ አይደለም።በቀዝቃዛዉ ጦርነት ወቅት በሞስኮ ዋሽግተኖች የሚተወን የዉሎ አምሽቶ ድራማ አይነት ነበር።


በፕሪስተን ዩኒቨርስቲ የዓለም አቀፍ ሕግ ፕሮፌሰር ሪቻርድ ፋልክ አንዱን ያስታዉሳሉ።ሉዊስ ፖሳዳ ካሪለስ ዛሬ የሰማንያ አምስት አመት አዛዉንት ናቸዉ።የካሊፎርኒያ ነዋሪ፥ ኩባዊ፥ ቬኑዙዋላዊ አሜሪካዊ ናቸዉ።ድሮ-በተማሪነቱ በእድሜ አንድ ዓመት የሚበልጠዉ የፊደል ካስትሮ ወዳጅ ብጤ ነበር።ኋላ ጠላት ሆኑ።


በ1963 (ዘመኑ በመሉ እንደ ጎርጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር ነዉ) የአሜሪካዉ ማዕከላዊ የሥለላ ድርጅት (CIA በእንግሊዝኛ ምሕፃሩ) የማሸበር፥ የመግደልና የመሻጠር ሙያ አሰለጠነዉ።ከእንግዲሕ አንቱ ናቸዉ።ፖሳዶ ካስትሮን ለመግደልና ለማስገደል በተደጋጋሚ ሞክሩ።በተፈጥሮ ያዳበሩት ድፍረት፥ ጥላጫ፥ ከአሜሪካኖች የቀሰሙት ዕዉቀት፥ መሳሪያ ገንዘብም ብዙ አልፈየዳቸዉም።ሰዉዬዉ አልተገኙም።ፖሳዳም ደም-ለማፍሰስ ማድባታቸዉን አልተዉም።
A protester wearing a Guy Fawkes mask holds a paper-made mock TV camera during a demonstration against the National Security Agency (NSA) and in support of U.S. whistleblower Edward Snowden, outside the Dagger Complex, which is used by the U.S. Army intelligence services, in Griesheim, 20 km (12.4 miles) south of Frankfurt, July 20, 2013. REUTERS/ Kai Pfaffenbach (GERMANY - Tags: POLITICS CIVIL UNREST CRIME LAW TPX IMAGES OF THE DAY)የሥለላዉን ድርጅት በመቃወም


1976 ሰላዩ ለካስትሮና ለተከታዮቻቸዉ ያነጣጠሩትን የጥፋት ለበቅ ተራ-ወገኖቻቸዉ ላይ ሊያወርዱት ወሰኑ።የበረራ ቁጥር 455 ፥ የኩባ የመንገደኞች አዉሮፕላን ወደ ኪንግሰቶን-ጃማይካ ሊበር ከባርቤዶስ አዉሮፕላን ማረፊያ ተነሳ።ብዙም አልቆየ።ጋየ።ሰባ-ሁለት መንገደኞቹም ከሰሉ።


የየዋሕ መንገደኞች ቤተሰቦች፥ ዘመድ፥ ወዳጆች፥ ሲላቀሱ፥የብዙዉ ዓለም መንግሥታት ሽብሩን ሲያወግዙ የሲ አይ ኤዉ ጀግና ተደሰቱ።ዩናይትድ ስቴትስም አሸባሪ ጀግናዋን እጇን ዘርግታ ተቀበለችዉ።ዘንድሮ በሰላሳ ሰባት ዓመቱ የሰላሳ ዓመቱ አሜሪካዊ ሰላይ ኤድዋርድ ስኖደን ከሐዋይ በሆንግ ኮንግ አድርጎ ሞስኮ ገባ።


ስኖደን አንድም ሰዉ አልገደለም።ለመግደልም አልሞከረም።ገንዘብ አልዘረፈም።ለመዝረፍም አልሞከረም።የታላቂቱን ሐገር ትልቅ ደባና ሚስጥር ግን በርግጥ አጋለጠ።እና ፖሳዳና ብጤዎችን አሸባሪዎች የምትንከባከበዉ፥ትልቅ ሐገር ትንሹን የቀድሞ ሰላይዋን ለመያዝ በትላልቅ ጥፍር ጥርሶቻ መንግሥታትን ትቧጭር፥ ትናከስ ያዘች።


«እኔ አሁንም የምጠብቀዉ ሩሲያም ሆነች፥ ሌሎች ለሚስተር ስኖደን፥ ጥገኝነት ለመስጠት እንፈልጋለን የሚሉ ሐገራት የዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ አካል መሆናቸዉን ይገነዘባሉ፥እና ለዓለም አቀፉ ሕግ መገዛት አለባቸዉ ብዬ ነዉ።»


ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ፥ ዓለም አቀፍ ሕግ ትርጉም ብያኔ እንዴትነት ሁሌም እንዳወዛገበ፥ እንዳነጋገረ በጉልበተኞች ልክ የሚሰፋ-ወይም የሚጠብ ነዉ።የድፍን ዓለም ማሕበራት፥ የዜጎች፥ የፖለቲከኞች፥ የሙሕሯን፥ የጋዜጠኞችን፥ የደራሲዎችን፥ የጦር መኮንኖች ወዘተ የስልክ ንግግር፥ የኢሜይል ልዉዉጥ፥ ባንዲት ሐገር እንዲቀዳ፥ እንዲከማች፥ ለተፈለገ ወገን እንዲሰጥ የፈቀደ ዓለም አቀፍ ሕግ፥ ዓለም አቀፍ ማሕበረሰብስ ካለም ዓለም አቀፉ ጉልበት፥ ሐብት፥ ወይም ለሕግ አለመገዛት መሆን አለበት።


ከቀዝቃዛዉ ጦርነት ፍፃሜ በሕዋላ የዓለምን የልዕለ-ሐይልነት ጉልበት ጠቅላላ የያዘችዉ ዩናይትድ ስቴትስ እንደ ጦር ጉልበቷ፥ እንደ ሐብቷ ሁሉ በስለላዉም የሚስተካከላት የለም።NSA በሚል ምሕፃረ-ቃል የሚጠራዉ ብሔራዊ የፀጥታ ድርጅት ሠላሳ አምስት ሺሕ ቋሚ ሠራተኞች አሉት።
Bildnummer: 59982415 Datum: 03.07.2013 Copyright: imago/Christian Ohde
Kopfhörer mit USA-Fahne auf einem Tisch, Symbolfoto Abhörskandal Prism Symbolfoto Abhörskandal USA xcb x0x 2013 quer Abhörprogramm Abhörprogramme Computerprogramm Computerprogramme Datensammlung Kontrolle NSA Prism Spionage Spionageprogramm Spionageprogramme Spähprogramm Spähprogramme Symbolbild Symbolbilder Symbolfoto Symbolfotos ausspähen kontrollieren online spionieren von Späh-Skandal Spähaktion Spähaktionen Abhörskandal Abhörskandale Abhör-Skandal abhören Kopfhörer mithören Zahlencode binär binärer Binärcode USA-Fahne US-Fahne Fahne Flagge 
59982415 Date 03 07 2013 Copyright Imago Christian Ohde Headphones with USA Flag on a Table Symbolic image Wiretapping scandal Prism Symbolic image Wiretapping scandal USA x0x 2013 horizontal Computer program Computer programs Data collection Control NSA Prism Espionage Symbol image Symbol Pictures Symbolic image Icon photos Spying control Online Spy from Scandal Wiretapping scandal Interception Scandal Interception Headphones Listening Numeric code binary binary Binary code USA Flag U.S. Flag Flag Flagየሥልክ ጠለፋ ምሳሌ
የስኖደን ብጤ የኮንትራት ሠራተኞች ቁጥር ከቋሚዎቹ አይተናነስም።ሥለ NSA የተለያዩ መፅሐፍት ያሳተመዉ ጋዜጠኛ ጀምስ ባምፎርድ እንደሚለዉ፥ እርስዎ ከዱባይ ወይ ከለንደን አዲስ አበባ ላለች ፍቅረኛዎ የፍቅር ኢሜል ይመይላሉ እንበል።ስኖዳን እና ብጤዎቻቸዉ ሐዋይ፥ ሜሪላንድ ወይም የፈለጉበት ቦታ ሆነዉ-ከፍቅረኛዎ እኩል ምናልባትም ቀድመዉ ኢሜልዎን ያነባሉ።

«በኢንተርነት የሚደረገዉ ከዘጠና ዘጠኝ በመቶ በላይ ግንኙነት አንድም ወደ አሜሪካ ይገባል አለያም በአሜሪካ በኩል ያልፋል።ሥለዚሕ ዩናይትድ ስቴትስ ከፍተኛ አቅም አላት።መቼም እንዲሕ አይነቱን አቅም ኔዘርላንድስ ወይም ሌላ የአዉሮጳ ሐገር ይኖረዋል ብለሕ አትጠብቅም።»


ሥልክ የደዉሉት ከጂዳ፥ የተደወለልዎት ካፓርስ ነዉ እንበል።ወዴትም ይደዉሉ፥ ከየትም ይደወልዎት ከሰማንያ ከመቶ የሚበልጠዉ የሥልክ ንግግር በአሜሪካ በኩል ነዉ የሚያልፈዉ።


«በስልክ ንግግርም ቢሆን ከሰማንያ በመቶ የሚበልጠዉ በአሜሪካ በኩል ነዉ የሚተላለፈዉ።ሥለዚሕ ዩናይትድ ስቴትስ የዓለምን ግንኙነት ለመምጠጥ ከፍተኛ ዕድል አላት።»


አሜሪካን ሳይነካ የሚያልፈዉን የሥልክ ጥሪ እነ ስኖደን ከያለበት ጠላልፈዉ፥ ለቃቅመዉ ከዚያ የመረጃ ትልቅ ጎተራቸዉ ያክቱታል።ከዚያ እያስተረጎሙ፥ እያስተነተኑ ለአለቆቃቸዉ ያቀርባሉ። እርስዎ ተራ ሰዉ ነዎት።በNSA አይን ግን የጀርመንዋ መራሒተ-መንግሥት አንጌላ ሜርክልም ከርስዎ መለየታቸዉን እራሳቸዉ እንዳሉት እርግጠኛ አይደሉም።
Bildbeschreibungen: Bei seinem ersten öffentlichen Auftritt traf sich Edward Snowden am Freitag, den 12 Juli 2013 auf dem Moskauer Flughafen Scheremetjewo mit Menschenrechtlern und Anwälten. Der US-Amerikaner möchte in Russland bleiben, solange er nicht nach Südamerika ausreisen kann.
Menschenrechtsbeauftragter der RF Wladimir Lukin inmitten der Journalisten.
Foto: Jegor Winogradow / DWስኖደን ከመብት ተሟጋቾች ጋር


«እኔ እራሴ የሥልክ ንግግሬ የት እንደተቀዳ አላዉቅም።ባዉቅ ኖሩ ለፓርላማዉ ኮሚቴ አናገር ነገር።»


ለዩናይትድ ስቴትስ ኢራን፥ ሶሪያ፥ ቬኑዙዌላ፥ ቦልቪያ፥ ኢኳዶር የቅርብ ክትትል የማይለያቸዉ «ጠላቶች» ናቸዉ።ብራዚል «ወዳጅ» ናት።ከካራካስ ባለሥልጣናት፥ እኩል የብራዚሊያ ሹማምንት፥ ከቦሊቢያ ዜጎች እኩል የብራዚሎች ንግግር፥ ፅሁፍ፥ እየተጠለፈ፥ እንቅስቃሴያቸዉ እየተቀዳ ይጠራቀማል።


ለዋሽግተኖች፥ ሞስኮዎች ወይም ቤጂንጎች የቀዝቃዛዉ ጦርነት ዘመን ጠላት ናቸዉ።አሁን ደግሞ በተለይ ቻይና የምጣኔ ሐብት ተፎካካሪ፥ የዓለም አቀፍ መርሕ ተፃፃራሪ ናት።የጆርጅ ደብሊዉ ቡሽ መስተዳድር የባግዳድን ቤተ-መንግሥት ያስረከባቸዉ የኢራቅ የሺዓ ፖለቲከኞች አፍ-አይ’ናቸዉ ከአዋሽግተኖች፥ ልብ ቀልባቸዉ ደግሞ ከቴሕራኖች ጋር ነዉ ይባላል።ለክፉዉም ለደጉም በቅጡ መሰለል አለባቸዉ።


ጀርመን ባንፃሩ የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት አባል፥የዩናይትድ ስቴትስ የቅርብ ተሻራኪ ጥብቅ ወዳጅ ናት።ግን ስኖደን ያጋለጠዉ መረጃ እንዳመለከተዉ ጀርመኖች ከቻይኖች እና ከኢራቆች እኩል ይመረጃሉ።ለጀርመኖች በርግጥ አስደንጋጭ ነዉ።ጋዜጠኛና የስለላ መፅሐፍት ደራሲዉ ጄምስ ባምፎርድ እንደሚለዉ አሜሪካኖች ጀርመን ላይ የጨከኑት ጀርመኖች የአሜሪካ «ጠላት» ሥለሆኑ አይደለም ባይ ነዉ።


«ጀርመን በብዙ ምክንያት የአሜሪካንን ትኩረት ትስባለች።አንደኛዉ ምጣኔ ሐብታዊ ነዉ።ጀርመን የአዉሮጳ የምጣኔ ሐብት ዋና ማዕከል ናት።ሁለተኛዉ የመስከረም አንዱ የአሸባሪዎች ጥቃት የተጀመረዉ ከጀርመን ነዉ።ሰወስተኛዉ ጀርመን አዉሮጳ ዉስጥ ምጣኔ ሐብታዊ ብቻ ሳይሆን ፖለቲካዊ ተፅዕኖም ታሳርፋለች።ሥለዚሕ የጀርመንን ንግግር ማድመጥ ማለት የኔዘርላንድስ፥ የስጳኝ፥ የግሪክ የሌሎችንም የአዉሮጳ ሐገራት እንቅስቃሴን በዚሕ በሚስጥር መገናኛ ዘዴ አማካይነት ማወቅ ማለት ነዉ።»


ጀርመኖችን በመሠለሉ ሒደት የጀርመን መንግሥት ባለሥልጣናት በተለይም የሐገሪቱ ፌደራላዊ የሥለላ ድርጅት (ቡንደስ ናኽሪሽተን ዲኒስት) መሪዎች ከአሜሪካኖች ጋር ተባብረዋል የሚለዉ ዘገባ የጀርመን ፖለቲከኞችን እያወዛገበ ነዉ።የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች የሥለላዉ ተቋም ባለሥልጣናት ከሥልጣን መዉረድ አለባቸዉ እስከማለት ደርሰዋልም።


የአገር አስተዳደር ሚንስትር ሐንስ ፔተር ፍሬድሪሽ አሜሪካኖች ጀርመንን ሥለመሠለላቸዉ ማብራሪያ እንዲሰጧቸዉ ዋሽግተን ድረስ ሔደዉ ጠይቀዉ ነበር።የተቃዋሚ ፓርቲዎችን ጥያቄና ጥርጣሬ የሚያስወግድ መልስ ግን አልሰጡም።ወይም አላገኙም።መራሒተ መንግሥት አንጌላ ሜርክልም የአሜሪካ ሠላዮች የጀርመንን ሕግ ሥለ መጣስ-አለመጣሳቸዉ የማዉቀዉ ነገር የለም ባይ ናቸዉ።
Barack Obama telefoniert im Oval Office
picture alliance / Photoshotኦባማ
«የጀርመንን ሕግ አለማክበራቸዉን የሚያረጋግጥ መረጃ የለኝም።ባለሙያዎቻችን ይሕን ጉዳይ እንዲያጣሩ ለነሱ እንተወዋለን።ባስቸኳይ መታወቅ አለበት።በዚሕ ሒደት የአገር አስተዳደር ሚንስትሩና የምክር ቤቱ ልዩ ኮሚቴ የሚያጠናክሩትን ዘገባ ካየን በኋላ መወሰድ ሥላለበት ጉዳይ እናጤናለን።ለወደፊቱ ግን በምንም መንገድ የጀርመን ሕግ መጠበቅ አለበት።»

ጀርመኖችን ከጀርመኖች የሚያጨቃጭቀዉ የሥለላ ቅሌት አሜሪካኖችን ከሩሲያዎች፥ ጋር እያወዛገበ ነዉ።የፕሬዝዳት ባራክ ኦባማ ቃል አቀባይ ጄ ካርኒ ልክ እንደ ኦባማ ሁሉ ሩሲያ የቀድሞዉን አሜሪካዊ ሠላይ ለአሜሪካ አሳልፋ መስጠት አለባት ይላሉ።


«ከቦስተኑ ማራቶን የቦምብ ጥቃት በኋላ ከሩሲያ ጋር ያለንን የተጠናከረ ትብብር ከግምት በማስገባት እና በሩሲያ ጠያቂነት ከፍተኛ ወንጀል የፈፀሙ ሰዎችን አሳልፈን መስጠታችንን ጨምሮ፥ ሕግን በማስከበሩ መስክ ለረጅም ጊዜ ካለን ትብብር አኳያ የሩሲያ መንግሥት ሚስተር ስኖደንን ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ያባርራሉ ብለን እንጠብቃለን።»


የቦሊቪያዉ ፕሬዝዳት ኢቮ ሞራሌስ ሞስኮ የገቡት ሞስኮ-ዋሽግተኖች ጠጣር ቃላት ሲወራወሩ ነበር።ድፍን ዓለምን የሚሰልለዉ የልዕለ-ሐያሊቱ ሐገር ግዙፍ የሠላላ ባለሙያዎች ፕሬዝዳት ሞራሌስ ታዳኙን ሠላይ ኤድዋርድ ስኖደንን ባዉሮፕላናቸዉ ይዘዉ ወደ ሐገራቸዉ ሊመለሱ ነዉ አሉ።የዩናይትድ ስቴትስን ቁጣና ግልምጫ የሚፈሩት የፈረንሳይ፥ የስጳኝ፥ የፖርቱጋልና የኢጣሊያ መንግሥታት የሞራሌስ አዉሮፕላን በአየር ክልላቸዉ እንዳይበር አገዱ።


የኦስትሪያ ባለሥልጣናት አዉሮፕላኑን አሳርፈዉ ፈተሹ።ሶኖደን አልነበረም።የደቡብ አሜሪካ መንግሥታት እንደ ብዙዉ ዓለም መንግሥታት በአሜሪካ በመሠለላቸዉ ኦባማ «ዓለም አቀፍ» በሚሉት ሕግ መሠረት እንክሰስ አላሉም። ቢሉም የሚሰማቸዉ የለም። ከፕሬዝዳንታቸዉ አንዱ በሐሰት መረጃ ለአዉሮፕላን አደጋ መጋለጣቸዉን ግን አልታገሱትም።አወገዙት።


ቁጣ ዉግዘቱ ግን ከአፍታ የመገናኛ ዘዴዎች ዜናነት አላለፈም።የፕሬዝዳት ቭላድሚር ፑቲን አፀፋ እንደ ጀርመኖች-በአገም ጠቀም፥ እንደደካማዎቹ የደቡብ አሜሪካ ሐገራት ባፍታ ቁጣ የሚያበቃ አይነት አይደለም።


«እኛ እንደሌሎች መንግሥታት አናጎበድድም።ሩሲያ የራስዋ ነፃ የዉጪ መርሕ አላት።ይሕ መርሐም በዚሁ ይቀጥላል።ወዳጆቻችን ይሕን አጢነዉ አደብ ቢገዙ ጥሩ ነዉ።ከሥለላ ዉዝግብ ይልቅ የአሜሪካና የሩሲያ ግንኙነት በጣም አስፈላጊ ነዉ።»
Russian Prime Minister Vladimir Putin visits the Far Eastern State University in Vladivostok, about 9,300 kilometers (some 5,750 miles) east of Moscow, on Monday, Sept. 1, 2008. A portrait of Czar Nicholas II is at left. (AP Photo/ RIA Novosti, Alexei Druzhinin, Pool )ፑቲን


አሜሪካኖች ግን አላረፉም።በመጪዉ ነሐሴ ማብቂያ ሩሲያ በምታስተናግደዉ የቡድን ሃያ አባል ሐገራት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ፕሬዝዳት ኦባማ እንዳይካፈሉ ወግ አጥባቂዎቹ የአሜሪካ ፖለቲከኞች እየጎተጎቱ ነዉ።ቬኑዙዌላ፥ የኢኳዶር እና የቦሊቪያ መንግሥታት ሞስኮ አዉሮፕላን ማረፊያ «ለታገተዉ» የቀድሞ የአሜሪካ ሠላይ ጥገኝነት ለመስጠት በመፍቀዳቸዉ ከዋሽግተን የሚሰነዝርባቸዉ የቅጣት ዛቻ፥ ማስፈራሪያም እንደቀጠለ ነዉ።እኛ ለዛሬዉ ከዚሕ በላይ መቀጠል አንችልም።ነጋሽ መሐመድ ቸር ያሰማን።


ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ

Deconstructing Construction Corruption in Ethiopia

Alemayehu G Mariam
corruption ahead
 In my fifth commentary on corruption in Ethiopia this year, I focus on the construction sector. The other commentaries are available at my blogsite.
The cancer of corruption in the construction sector the World Bank (WB) documented in its “Diagnosing Corruption in Ethiopia” is just as malignant and metastatic as in the land, education and telecommunications sectors. According to the WB report:
In the construction sector, Ethiopia exhibits most of the classic warning signs of corruption risk, including instances of poor-quality construction, inflated unit output costs, and delays in implementation. In turn, these factors appear in some cases to be driven by unequal or unclear contractual relationships, poor enforcement of professional standards, high multipliers between public sector and private sector salaries, wide-ranging discretionary powers exercised by government, a lack of transparency, and a widespread perception of hidden barriers to market entry.
Ethiopia’s “construction sector” falls into four categories: roads, water supply and irrigation, power, and other public works including construction of universities, schools, hospitals and markets. Annual spending on roads alone is estimated to be US$1.2 billion. The “government” totally dominates the construction sector. “Ethiopia is unusual compared with most other African countries, which have already fully privatized the design and construction of public works.”
There are multiple and “interrelated drivers of corruption in Ethiopia’s construction sector.” These drivers are “related to deficiencies in accountability (transparency based on clear performance criteria), capacity (availability of sufficient material and human resources and proper procedures), and trust (confidence in the market that allows businesses to invest in increasing their own capacity). In Ethiopia, “A lack of capacity makes corruption possible, a lack of accountability makes corruption happen, and a lack of trust allows corruption to take root.”
The WB report highlights corruption in Ethiopia’s construction sector along six dimensions. The policymaking and regulatory processes are at high-risk area of corruption. Such corruption has a major effect on sector governance.” Policies and regulations could “encourage, or help hide, corrupt practices” and unless corrected perpetuate corruption by groups or individuals. The Ethiopian “government” “controls the price of construction materials, access to finance, and access to equipment. It controls professional and company registrations. It maintains high-level, bilateral infrastructure deals with China and lacks independent performance audits.” According to the WB report, “Many stakeholders are concerned about the possibility of a connection between the dominant role of Chinese contractors in the road sector and high-level links between the Ethiopian and Chinese governments” and the “lack of effective competition, with Chinese contractors dominating the international market and a limited set of domestic contractors dominating the national market.” These problems are compounded by other factors such as poor quality control, weak enforcement of professional standards and overall lack of transparency. Professionals in the construction sector are reluctant to complain “for fear of being victimized” and believing there is no truly independent body to which they can appeal.” Since the “government is a major client”, “there is a reluctance to express dissent.”
The planning and budgeting (P&B) process is the second area of high corruption in Ethiopia’s construction sector.  When planning and budgeting “deviates from the use of a rational, objective basis for prioritizing the allocation of limited resources on the basis of need, anticipated rates of return, or other objective criteria,” it opens the floodgates of corruption. In Ethiopia, the P&B process is characterized by “lack of separation between policy making, budget allocation, and implementation functions” and “top-down planning by decree.” There are instances in which “projects that are not responding to a prioritized need and (when combined with weak procurement regulations) can sometimes be negotiated directly between a  corrupt official and a specific construction company.” Corruption also occurs in the form of “adoption of inappropriately high construction standards to enhance contract values, construction of new infrastructure while neglecting to maintain existing facilities, conflicts of interest for officials with a stake in the construction sector” and aiding “construction companies with party political allegiances.”
The third area of corruption is found in management and performance monitoring . According to the WB report, management weaknesses can lead to corruption in three main ways: “(a) Without basic good management controls, individuals (whether working for the client, the consultant, or the contractor) can find themselves free to take shortcuts that may cross the line into corruption. (b) Without good data management and reporting systems, the management information needed to identify and address corruption does not exist. (c) If the management is so incompetent that it gives rise to administrative or technical obstacles that are otherwise impossible to address, corrupt activities may be seen as the only realistic way for otherwise professionally minded individuals to deliver results.” In Ethiopia such corruption occurs for a number of reasons including “low remuneration of some managers and procurement staff”, “shortlisting of poorly performing companies and companies without capacity for new work”, “difficulty of obtaining public information about contracts,” and “lack of independent professional bodies and weak enforcement of professional standards”, among others.

Thursday, July 18, 2013

Tuesday, July 16, 2013

Ethiopian Police Detain Activists Calling for Terror Law Repeal

By William Davison 


Ethiopian police detained 42 opposition supporters distributing leaflets calling for the repeal of an anti-terrorism law they say has been used to stifle dissent, the Unity for Democracy and Justice party said.
The arrests in four districts of the capital, Addis Ababa, occurred yesterday as UDJ members distributed pamphlets asking people to sign a petition that also demands the release of jailed opposition members, religious leaders and journalists, the party said in an e-mailed statement.
“It is harassment,” UDJ Chairman Negasso Gidada said in a phone interview today from the capital. “There is no law that says you need permission to distribute leaflets.”
The mobile phones of government spokesman, Shimeles Kemal, and Bereket Simon, spokesman in the prime minister’s office, were switched off when called for comment. The opposition campaigners were released on bail late yesterday and the group plans to continue gathering signatories for the petition, Negasso said.
Opposition politicians and reporters have been arrested under an anti-terror law passed by Ethiopia in 2009. The U.S. and United Nations have criticized the legislation for curbing freedom of expression after the arrest of several journalists.
Online writer Eskinder Nega and Woubshet Taye, former deputy editor of the defunct Awramba Times, were convicted last year under the law for crimes including trying to incite anti-government protests and having links to terrorist organizations.
Ethiopia’s 547-member parliament has one opposition-party member.
UDJ held demonstrations on July 14 in two cities to protest the lack of democratic rights under the current government and it is planning to hold more events through September, including in Addis Ababa, Negasso said.
Its “Millions of Voices for Freedom” campaign follows a public protest in the capital last month by the opposition Blue Party that was the largest demonstration by a political party since 2005 when opposition supporters protested election results.
To contact the reporter on this story: William Davison in Addis Ababa via Johannesburg atpmrichardson@bloomberg.net.
To contact the editor responsible for this story: Antony Sguazzin at asguazzin@bloomberg.net.

Monday, July 15, 2013

Ethiopian anti-terrorism law faces opposition - Al Jazeera Video


Opposition parties in Ethiopia are stepping up their push to scrap a controversial anti-terrorism law.They say it is flawed and aimed at silencing the government's critics.There are hundreds of political prisoners in Ethiopian jails, including ten journalists.Al Jazeera's Catherine Soi reports from Addis Ababa.



በቂልንጦ እስርቤት የእሰረኞች ደም በድብደባ እንደጎርፍ መፍሰሱን የአይን እማኞች ተናገሩ

ሐምሌ ፰( ስምንት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም


ኢሳት ዜና :- አርብ ፣ ሀምሌ 6 2005 ዓም በእነ አቶ ተሻለ ኮርኔ መዝገብ የተከሰሱ 69 የኦሮሞ ተወላጆች ፍርድ ቤት መቅረብ ሲገባቸው፣ ፍርድ ቤት የሚወስዳቸው ፖሊስ ያጣሉ። በቅጽል ስሙ ሻእቢያ እየተባለ የሚጠራውን የእስር ቤቱን ሀላፊ ሲጠይቁት ቀጠሮአቸው ለ4 ወር መራዘሙን ይነግራቸዋል። እስረኞቹም ” ከ2 አመታት በላይ የላፍትህ ታስረን በመጨረሻ ብይን በሚሰጥበት ወቅት ለ4 ወራት ተራዝሟል መባሉ ተገቢ አይደለም” በማለት ለጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ የሚላክ ፊርማ ማሰባሰብ ሲጀምሩ ማረሚያ ቤቱ መረጃው ይደርሰውና 69ኙ እሰረኞች በ20 ተከፋፍለው ወደ ተለያዩ የማረሚያ ክፍሎች ወይም ዞኖች እንዲበተኑ ይደረጋል።

አርብ ጧት ሌሎች እስረኞች ወደ ውጭ እንዳይወጡ ከተደረገ በሁዋላ ፣ ሻእቢያ በሚባለው የእስር ቤቱ ሀላፊና ከውጭ በመጡ የፌደራል ፖሊስ አባላት እንዲደበደቡ ይደረጋል። አስተባባሪ ናቸው የተባሉትን 18 እስረኞችን እንደገና በማውጣት በሰደፍና እና በዱላ ከቀጠቀጡዋቸው በሁዋላ 8ቱ ራሳቸውን ሲስቱ ወደ እስር ቤቱ የህክምና ክፍል ይወሰዳሉ። ችግሩ ከአቅሙ በላይ መሆኑን የእስር ቤቱ የህክም ክፍል በመግለጹ፣ በአምቡላንስ ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል




የአይን እማኞች ለኢሳት እንደገለጹት እስረኞቹ የተደበደቡበት ቦታ በደም በመጨቅየቱ አርብ እለት በውሀ ሲታጠብ አርፍዷል።

ከፍተኛ ጉዳት ከደረሰባቸው መካከል በላይ ኮርሜ ፣ ተፈሪ ቀብኔሳ እና መንግስቱ ግርማ የሚባሉ ይገኙበታል።

በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸው የአህኮ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና እሰረኞቹ መደብደባቸውንና የተወሰኑት ሆስፒታል መግባታቸውን መረጃው እንደደረሳቸው ገልጸዋል።

ዶ/ር መረራ “ድርጊቱን በተደጋጋሚ ለመንግስት አመልክተን መልስ በማጣታችን መንግስት ሆን ብሎ በፖሊሲ ደረጃ ይዞ የሚያካሄድ ይመስላል” ሲል አክለዋል።

የእስር ቤቱን ሀላፊዎች ለማግኘት ሙከራ ብናደርግም አልተሳካልንም።

ተቃዉሞ ሠልፍና የኢትዮጵያ ፖለቲካ

የተቃዉሞ ሠልፍ መደረጉን፥ አንዳዶች ገዢዉ ፓርቲ ላለፉት ስምንት ዓመታት ይከተለዉ ከነበረዉ መርኹ የመለሳለሱ ምልክት ይሉታል።ተቃዋሚ ፓርቲዎች የመጠናከራቸዉ ማሳያ ነዉ-ባዮችም አሉ። ሌሎች ደግሞ ቢያንስ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን የሚደግፈዉ ሕዝብ ተቃዉሞዉን ለማሰማት ዶክተር ነጋሶ እንዳሉት የመቁረጡ አብነት ነዉ።
ደሴና ጎንደር፥ትናንት..... ተቃዋሚ ሠልኛዉ.... ከሠልፉ አደራጆች አንዱ....

«ከእነዚሕ ሠልፈኞቹ አብዛኞቹ እስላማዊ ፅንፈኞች ናቸዉ» የኢትዮጵያ መንግሥት ቃል አቀባይ ለአዣንስ ፍራንስ ፕረስ ዜና ወኪል።

የፖለቲካ ተንታኝ።የተቃዉሞ ሠልፉ መነሻ፥ እስከ ሠልፉ የነበረዉ ሒደት ማጣቃሸ፥ እድምታዉ መድረሻችን ላፍታ አብራችሁን ቆዩ።

ኢትዮጵያ ዉስጥ የ1997 ቱ አጠቃላይ ምርጫ የመቶዎችን ሕይወት ባጠፋ ደም አፋሳሽ ግጭት ካሳረገ ወዲሕ የሐገሪቱን መንግሥት የሚቃወም የአደባባይ ሠልፍ ሲደረግ የትናንቱ ሁለተኛዉ ነዉ። የመጀመሪያዉ ሠማያዊ ፓርቲ ያዘጋጀዉ የተቃዉሞ ሠልፍ ነበር። ባለፈዉ ግንቦት አዲስ አበባ ተደረገ።የትናንቱን ሠልፍ የጠራዉ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ (አንድነት ባጭሩ) ፓርቲ ነዉ።

በግንቦቱም በትናንቱም ሰልፎች የተሳተፈዉ ሕዝብ ያነሳቸዉ ጥያቄዎች ብዙ ግን ተመሳሳይ ናቸዉ።
ሕገ-መንግሥቱ ይከበር።በፀረ-ሽብር አዋጅ ወይም ደንብ ሰበብ የታሠሩ ፖለቲከኞች፥ የሐይማኖት መሪዎች እና ጋዜጠኞች ይፈቱ።የዜጎች ሠብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ይከበሩ።እና ሌሎችም። አንድነት እንደዚሕ አይነት አጠቃላይ ብሔራዊ ጥያቄዎችን ያዘሉ የአደባባይ ተቃዉሞ ሠልፎችን ከርዕሠ-ከተማ አዲስ አበባ ይልቅ ጎንደርና ደሴ የጠራበት ምክንያት ሠልፉ ከመደረጉ እኩል እያነጋገረ ነዉ።የፓርቲዉ ፀሐፊ አቶ አስራት ጣሴ መልስ አላቸዉ።
Auf dem Bild:
Plakat auf der Andinet Party von UDJ.
Foto: Yohannes Gebreegziabher / DW 
20.06.2013 
Äthiopien, Andinet


የአንድነት ፓርቲ ፕሬዝዳት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳም ፓርቲያቸዉ ለሠወስት ወር የነደፈዉ የአደባባይ ተቃዉሞ ሠልፍ፥ ፊርማ የማሰባሰብ፥ እና ሕዝባዊ ሰብሰባ ማድረጉን ይቀጥላል።

እኒያ ዲሞክራሲያዊ የሚባሉት የምዕራብ ሐገራትን በርግጥ ለሰላማዊ የተቃዉሞ ሠልፍ፥ ለንንፅር መጠቅሱ አይመችም።ባለፉት ጥቂት አመታት ቱኒዚያ፥ ግብፅ፥ ቱርክ፥ ብራዚሎችም ቅሬታን፥ በአደባባይ ሕዝባዊ ሠልፍ መግለፅ-ሳይሆን አለመግለፅ እንግዳቸዉ እየሆነ ነዉ።

ለኢትዮጵያ ግን ተቃራኒዉ ነዉ-እዉነቱ።በተለይ ከ1997 ወዲሕ ሕዝብ መንግሥትን ተቃዉሞ አደባባይ መዉጣቱ አዲስ ነዉ።አዲሱ ወይም እንግዳዉ የተቃዉሞ ሠልፍ መደረጉን፥ አንዳዶች ገዢዉ ፓርቲ ላለፉት ስምንት ዓመታት ይከተለዉ ከነበረዉ መርኹ የመለሳለሱ ምልክት ይሉታል።ተቃዋሚ ፓርቲዎች የመጠናከራቸዉ ማሳያ ነዉ-ባዮችም አሉ። ሌሎች ደግሞ ቢያንስ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን የሚደግፈዉ ሕዝብ ተቃዉሞዉን ለማሰማት ዶክተር ነጋሶ እንዳሉት የመቁረጡ አብነት ነዉ።
Auf dem Bild:
Die Parteiführung von UDJ.
Foto: Yohannes Gebreegziabher / DW 
20.06.2013 
Äthiopien, Andinet
ISS በሚል ምሕፃረ ቃል የሚጠራዉ የአፍሪቃ የፀጥታ ጥናት ተቋም የፖለቲካ ተንታኝ አቶ ሐሌሉያ ሉሌ ከሰወስቱ አንዱን ለምረጥ ዋል አደር ብለን እንየዉ ይላሉ።ይሁንና በመጠኑም ቢሆን መንግሥት ለስለስ ማለቱን መጠቆሙ አይቀርም እንደ አቶ ሐሌሉያ እምነት።

የሠብአዊ መብት ተሟጋች እና የሕግ ባለሙያ አቶ ያሬድ ሐይለ ማርያም እንደሚሉት ደግሞ የሰወስቱም ድምር ዉጤት ነዉ-ማለቱ ይሻላል።

ጉዳዩ የሚመለከታቸዉን የመንግሥት ባለሥልጣናትን በሥልክ ለማነጋገር በተደጋጋሚ ሞክረናል።አንዱ ዉጪ ሐገር ናቸዉ።የተቀሩት ሥልካቸዉን አያነሱም።የመንግሥት ቃል አቀባይ አቶ ሽመልስ ከማል ለፈረንሳዩ ዜና አገልግሎት ለአዣንስ ፍራንስ ፕረስ ትናንት በሰጡት መግለጫ ግን በትናንቱ የተቃዉሞ ሠልፍ የተሳተፉትን «አብዛኞቹ ሙስሊም አክራሪዎች ወይም ፅንፈኞች ናቸዉ።» ብለዋለዋቸዋል። በዚሕም ምክንያት አቶ ሽመልስ ከማል፥ «መንግሥት ይሕ የተቃዉሞ ሠልፍ አያሳስበዉም።እነሱ (ሠልፈኞቹ) በሕይማኖት ጉዳይ የጥያቄ የሚገቡ እና ሐይማኖታዊ ጉዳዮችን ከፖለቲካ ጋር የሚቀይጡ ናቸዉ።»

መንግሥት ሰልፈኛዉና ጥያቄዉ ካላሳሰበዉ ሥለ ሠልፈኞቹ ፅንፈኝነት ለመግለፅ ያሰበበትን ምክንያት የሚያዉቁት በርግጥ አቶ ሽመልስ ብቻ ናቸዉ።ሠልፉ ግን የጎንደሩን ሠልፍ ባስተባበሩት በአቶ አሥራት ጣሴ አገላለፅ የግጭት «ኮሽታም» ያልተሰማበት-ሠላማዊ ነበር።

እስከ ሠልፉ ድረስ ፥ የአንድነት ፓርቲ በተደጋጋሚ እንዳስታወቀዉ በርካታ አባላቱ መታሰር፥ መታገት፥ መንገላታት ግድ ነበረባቸዉ።እስካሁን የታሠሩም አሉ። ሠልፈኛዉም አደባባይ እንዳይወጣ የተደረጉበትን የተለያዩ ማስፈራራቶችና እንቅፋቶችን መጋፈጥ ነበረበት።

በጫናዉ፥ በዉዝግብ፥ ዉግዘቱም መሐል ሠልፉ መደረጉ የፖለቲካ ተንታኝ ሐሌሉያ ሉሌ እንደሚያምኑት የኢትዮጵያ ፖለቲካ በዴሞክራሲያዊ አቅጣጫ የመንቀሳቀሱ፥ የሩቅም ቢሆን ጥሩ ምልክት ነዉ።


የሠብአዊ መብት ተሟጋቹ ያሬድ ሐይለ ማርያምም ተመሳሳይ ተስፋ አላቸዉ።

እና ዶክተር ነጋሶ እንዳሉት ወደፊትም ተቃዉሞን ባደባባይ መግለፁ «የፈለገዉ» ቢደርስ ይቀጥላል።
ሲሆን ለማየት ያብቃን።ነጋሽ መሐመድ ነኝ ቸር ያሰማን።
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ

AUDIOS AND VIDEOS ON THE TOPIC

Sunday, July 14, 2013

ከግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል ለቀረበልን ጥያቄ የተጠራ አስቸኳይ የስብሰባ


dceson
እንደሚታወቀው ውዷ ኢትዮጵያ አገራችን በዘረኛው፣ በአፋኙ እና በፋሽስቱ የTPLF/EPRDF አገዛዝ ቀንበር ስር ወድቃ በታሪኳ አጋጥሟት የማያውቅ የውርደት ማጥ ውስጥ ትገኛለች፣ በተለይ ከቀን ወደ ቀን በሕዝባችን ላይ እየተፈጸመ ያለው ዘግናኝ ግፍ እና በደል እየጨመረ የሰው አይምሮ ሊገምተው እና በቃላት ሊገለጽ የማይችል የመጨረሻ የስቃይ ደረጃ ላይ ደርሷል ድርጊቱንም የከፋ የሚያደርገው በገዛ ወገን ላይ ቀርቶ በጠላት ላይ ሊደረግ የማይታሰብ ዘር እና ሃይማኖት ሳይለይ በሁሉም የሕብረተሰብ ክፍል ላይ በእቅድ እየተከናወነ መሆኑ ነው::
በመሆኑም ይህ ግፍ አንገብግቧቸው ለአገራቸው እና ለህዝባቸው ነጻነት፣ ፍትህ ዲሞክራሲ ለማስፈን  የነጻነት ታጋዮች ወያኔን በለመደው ቋንቋ ለማናገር ቆርጠው ተነስተው ትግሉ የሚጠይቀውን መስዋእትነት በመክፈል ላይ ሲሆኑ በማያያዝም ይህንን የነጻነት ትግል በሁለንተናዊ መንገድ እንድንደግፍ ታሪካዊና ወቅቱን የጠበቀ የድጋፍ ጥሪ የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል አቅርቦልናል::
ስለዚህ በዚህ ጉዳይ ላይ ለመነጋገር እና ለጥያቄያቸው አፋጣኝ ወገናዊ ምላሽ ለመስጠት የድርጅታችንን አባሎች በሙሉ አስቸኳይ ስብሰባ ለመጥራት ተገደናል በመሆኑም ማንኛውም የድርጅታችን አባል አራተኛ ፎቅ በድርጅታችን ቢሮ ጎን ባለው የስብሰባ አዳራሽ እሑድ ጁን 30/2013 ከ14:00 ጀምሮ የምክክር ስብሰባ ላይ ተገኝተው መወሰድ ስላለበት ወቅታዊ አፋጣኝ ታሪካዊ ምላሽ አሳቦን እንዲሰጡ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ሲያስገነዝብ በማያያዝም በዚህ ስብሰባ ላይ የግድ አባላት በሙሉ እንዲገኙ ያሳስባል::
የስብሰባ ቀን: - እሑድ ጁን 30/2013
ስብሰባ ቦታ: - አራተኛ  ፎቅ በድርጅታችን ቢሮ ጎን ባለው የስብሰባ አዳራሽ
የስብሰባ ሰአት: - ከ14:00 ጀምሮ
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ
የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ
ኖርዌይ፣ ኦስሎ፥ ጁን 21/2013

በወያኔ መገዛት ይቁም!!

እስክንድር አሰፋ
ኦስሎ
14.07.2013
ሐገራችን ኢትዮጵያ በአንባገነኑ የወያኔ መንግስት በፍትህ መጓደል ና መዛባት ምክንያት ያለምንም ወንጀላቸው ዜጎመብታቸው በጠየቁ በየእስር ቤቱ ሃያ ሁለት አመታት ሲሰቃዩና ሲገድሉ ኖረዋል እየኖሩም ነው። እንዲሁም እንግልቱ ሲበዛባቸው ሐገራቸውንና ቀያቸውን ትተው እግሬ አውጪኝ በማለ በአረብ ሐገራት በአውሮፓ እንዲሁም በአሜሪካ ተበትነው ኖራሉ።

ከዛም አልፎ ተርፎ በየሄት ሐገር ሰርተው ለመኖር መከራቸውንና ስቃያቸውን ሲበሉ ይታያል፤ ሌሎችም እንዲሁ ያላደላቸው በበረሐና በባህር  ላይ ህይወታቸውን የሚያጡ  ንጹን ኢትዮጵያዊያንን  ቤቱ ይቁጠረው ። ለዚህ ሁሉ በደል ተጠያቂው  ዢው ወያኔ መንግስት ነው ።

የኢትዮጵያ ሕዝብ ለሁለት አስር ዓመታት በወያኔ የግፍ እና የጭቆና ስርዓት ውስጥ የኖረበት ጊዜ በቃኝ በማለት ለነጻነቱ እና ለዲሞክራሳዊ መብቱ መከበር ሲል ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ በዘር፣ በሃይማኖት፣ በቋንቋ እና በጾታ ሳይለያይ በወያኔ ስርዓት ላይ የተቃውሞ ድምጹን ማሰማት ይጠበቅበታል:: ግፍ፣ መከራ፣እና ስቃይ ይበቃል ማለት አለበት።

ለሐገራቸውና ለህዝባቸው በግንባር ቀደምትነት የሚሰዉ ጀግኖች ልጆች ዛሬም አሏት  ስለዚህ አሁን  በሐገር ውስጥም ሆነ በውጭ  ለጀመሩት  ሰላማዊ ትግል  ጊዜ ሳናጠፋ ልዩነታችንን ወደኋላ በመተው ጋሻ እንሁናቸው። እንዲሁም በውጪ ሆነው ከሚንቀሳቀሱ ሐይሎች  ጋር በመሆን  እንደ አስፈላጊነቱ  የሚጠበቅብንን ሐገራዊ ድርሻ መወጣት  ይኖርብናል።  

ስለዚህ የተጀመረውን ትግል ከመሪዎቻችን ጎን  በመቆም ግብ ላይ በማድረስ ወያኔን በምድረ ኢትዮጵያ ዳግመኛ እንዳያንሰራራ አድርገን በማስወገድ እኛንም ከስደት ሐገራችንንም ከውርደት እና ከውድቀት የምናድንበት ጊዜው አሁን  ነው። ኢትዮጵያ እጆቿን ዘርግታ ትጣራለች ድምጻቸው ለታፈነውና መብታቸው ለተረገጠው  ወገኖቻችን አለንላችሁ እንበላቸው። በወያኔ ስርአት መገዛት በቃ ብያለሁ!!!! እናንተስ?


ኢትዮጵያ ለዘላለም ተከብራ ትኑር
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ