Wednesday, August 31, 2016

የመኢአድ ጋዜጣዊ መግለጫ

የድርጅቱ ባለሥልጣናት በንባብ ባሰሙት ባለ-ሰባት ነጥብ የአቋም መግለጫ ያቀረቧቸዉ ጥያቄዎች ባስቸኳይ ካልተሟሉ ፓርቲያቸዉ ከሕዝብ ጎን ቆሞ በሰላማዊ መንገድ እንደሚታገል አስጠንቅቀዋል።
የመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ትናንት በሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ መንግሥት ፀጥታ አስከባሪዎች ለተቃዉሞ አደበባባይ በወጡ ሠላማዊ ሰልፈኞች ላይ የወሰዱትን የሐይል እርምጃ የግፍ ጭፍጨፋ በማለት አወገዘዉ።የኢትዮጵያ መንግሥት ሕገ-ወጥ በሚል ሽፋን የሠላማዊ ዜጎችን ቤት እያፈረሰ ነዋሪዎችን ማፈናቀሉን እንዲያቆምም ድርጅቱ ጠይቋል።የድርጅቱ ባለሥልጣናት በንባብ ባሰሙት ባለ-ሰባት ነጥብ የአቋም መግለጫ ያቀረቧቸዉ ጥያቄዎች ባስቸኳይ ካልተሟሉ ፓርቲያቸዉ ከሕዝብ ጎን ቆሞ በሰላማዊ መንገድ እንደሚታገል አስጠንቅቀዋል።
http://www.dw.com/am/የመኢአድ-ጋዜጣዊ-መግለጫ/a-19513038


ጌታቸዉ ተድላ ሐይለ ጊዮርጊስ
ነጋሽ መሐመድ
አዜብ ታደሰ


 Audios and videos on the topic

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለወቅቱ ሁኔታ

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር ኢሕአዴግ ሲነሣ ከነበረበት ሁኔታ አሁን ያለው ነባራዊ ሁኔታ የተለወጠ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ አስታውቀዋል፡፡


የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር የኢሕአዴግን ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴና የማዕከላዊ ምክር ቤቱን ጉባዔ ተከትሎ ለመንግሥታቸው መገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ “ኢሕአዴግ ግዙፉን የደርግ ሥርዓት በሚደመስስበት ጊዜ ካስቀመጣቸው እሤቶች መካከል እራስን ለሕዝብ የመስጠትና ለሕዝብ የመኖር ጉዳይ ወሣኝ ጉዳይ ነው ተብሎ የተያዘ ነው፤ ነገር ግን ነባራዊ ሁኔታው ተቀይሯል” ብለዋል፡፡


ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም “ነባራዊ ሁኔታው በተቀየረበት ሁኔታ አመራሩ የመንግሥትን ሥልጣን የሚያይበትና በተግባርም የሚፈፅምበት ሁኔታ በሚገባ ካልተቀየረ አሁን ባለንበት ደረጃ የጉዟችን እንቅፋትና መሠናክል የበዛበት ጉዞ ይሆናል” ብለዋል፡፡


ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡


http://amharic.voanews.com/pp/3487227/ppt0.html

Wednesday, August 17, 2016

የቨርጂኒያ ጉባኤ ውሳኔ መግለጫ





                   የቨርጂኒያ ጉባኤ ውሳኔ መግለጫ

           የህወሃት አጥፍቶ መጥፋት ፖሊሲ በተግባር ሲከሰት

ኢትዮጵያዊነት በተለያዩ ወቅቶች በስልጣን ላይ ያለው መንግሥት የዜጎችን መሠረታዊ መብት ሲጥስ፤ የሙስሊሙን ወገኖቻችንን ድምጽ ሲያፍንና መብታቸውን በሀይል ሲከለክል፤ በአረብ ሀገር ስለሚሰቃዩ ወገኖቻችን ብሶት፤ ስለአማራ ሕዝብ አላግባብ ከመሬታቸው መፈናቀልና ለሱዳን አላግባብ ስለሚሰጠው የኢትዮጵያ መሬት ተክታታይ መግለጫዎችን አውጥቶአል። አሁን ደግሞ ለሀገራችን ህልውና አስጊ ሁኔታ በመፈጠሩ ለየት ያለ መግለጫ ለማውጣት ተገዶአል። ይኅውም በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያውና ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ ፀረ ኢትዮጵያ የሆነው "መንግሥት" ከዳር እስከ ዳር በተነሳበት ሕዝባዊ ተቃውሞ ሊወድቅ የተንገዳገደበትና ተቃውሞውን በፍጹም አረመኔአዊ ጭካኔ በማዳፈን የፈጠረው ቀውስ ነው። በአሁኑ ወቅት ከዳር እስከ ዳር የሚታየውን የሕዝባችንን የእምቢተኝነትና፤ ለትግራይ ነጻ አውጭ ግንባር አንገዛም ባይነት በጥንቃቄ ገምግሞ ይኅንን መግለጫ አውጥቶአል።

በዘርና በቅዋንቅዋ የተዋቀረ ፌደራላዊ አስተዳደር የመጨረሻ ውጤቱ በሕዝብ መሀከል አለመግባባትን ፈጥሮ የእርስ በርስ ማጋጨትን የሚያስከትል መሆኑ ግልጽ ነው። በተለይም በሀገራችን ለዘመናት ሲገነባ የኖረውን የሕዝቡን የባህል፤ የአንድነትና የስነ ልቦና ትሥሥር በማዳከሙ አሳሳቢ ሁኔታ ላይ አድርሶታል። ከሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች በተሻለ መልኩ የተገነባውን አስተዳደር፤ የመከላከያና የብሄር አቀፍና የአንድነት እሴቶች ሀላፊነት በጎደለው መልኩ አፈራርሶታል። ይልቁንም የአንድ አካባቢ ተወላጆች በሚከተሉት የከፋፍለህ ግዛው መርህ መሠረት፤ በሀገሪቱ ያሉትን የሲቪል፤ የመከላከያ፤ የፀጥታና የኢኮኖሚ ቁልፍ መዋቅሮች እንዲቆጣጠሩ አድርጎአቸዋል። እንደዚሁም በአብዛኛው በሀገሪቲ ያሉትን የነጻ ገበያ ዘርፎች እንዲቆጣጠሩ ረድቶአቸዋል።

ዘረኛው መንግሥት ሕዝባችን ለሚያነሳቸው ሕጋዊና መሠረታዊ የመብት ጥያቄዎች ሁሉ እስካሁን የሚሰጠው ምላሽ የእሥር፤ የግድያና ከኖሩበት ቀየ ማፈናቀል ሆኖአል። በህዝባችን የሚቀርቡት የመብት ጥያቄዎች በዓለም መንግሥታት፣ በዓለም አቀፍ መብት ተኮር ድርጅቶች እንደዚሁም በዚሁ ዘረኛ የህወሃት/ኢህአዴግ ሕገ መንግሥት ላይ የሰፈሩና በሕግ የተደነገጉ መብቶች ናቸው። ሰሞኑን በጋምቤላ፡ በጎንደር፤ በባሕር ዳር፤ በኦሮምያ በአዲስ አበባ በኮንሶ በኦጋዴንና በመላው የሀገሪቱ ከተሞች በመካሄድ ላይ ያሉት ሰላማዊ ሰልፎች በቂ ምስክር ናቸው። ግድያው፤ አፈሳና ጭካኔ የተሞላበት ድብደባ የዚህ ዘረኛ አምባገነን መንግሥት ዓይነተኛ መገለጫዎች ናቸው።

የሀገራችንን ተጨባጭ ሁኔታ መረዳት ለመፍትሄው ወሳኝ እንደሆነ እናምናለን። የሥርዓቱ ደጋፊዎች አስተዳደሩ አንድ አንድ ጥገና ተደርጎለት ሊሻሻል እንደሚችል ሊሰብኩን ይሞክራሉ። 2

በዘር ላይ የተመሠረተ ፌድራሊዝምና አብዮታዊ ዲሞክራሲ ለሀገራችን የሶሽያልና የኢኮኖሚ ችግር መፍትሄ ያስገኛሉ ብለው ይሰብካሉ። የሀገሪቱ ቸግር የመነጨው ይኅንን ፍልስፍና በመከተል መሆኑን የተረዱት አይመስልም። በዘር ላይ የተመሠረተ የፌድራል አስተዳደር የሚሻሻል ሳይሆን ሥር ነቀል ለውጥ የሚያስፈልገው ነው። አለ የሚባለው የወያኔ ሕገ መንግሥትም ሕዝብ ያልመከረበትና በመሠረቱ የሀገሪቱንና የሀዝቦችዋን አንድነት የሚፃረር በመሆኑ የዲሞክራሲ መሠረት ሊሆን አይችልም።

ኢትዮጵያዊነት፤ የዜጎች መብት ማስከበሪያ ጉባኤ በተቃራኒው ሁለት መሠረታዊ መርሆዎችን ማለትም ሀ) ሁሉንም ዜጎች ያቀፈ ኢትዮጵያዊነትን ያራምዳል ለ) ዓለም አቀፍ እውቅናና ክብር ላላቸው ለመሠረታዊ የሰው ልጅ፤ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች መከበር ይታገላል። ድርጅታችን ባዘጋጀው " የዜጎች ቃል ኪዳን ለዲሞክሪያስያዊት ኢትዮጵያ" ሰንድ እንደተገለፀው ለዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ አስተማማኝ መሠረት በሚጥሉና የዜጎችን ሁለንተናዊ መብቶች በሚያስከብሩ መርሆዎች መመራት ወሳኝነት አለው። እነሱም፤ የኢትዮጵያ ግዛትና የሕዝቦችዋ አንድነት፤ የግለስብ ነጻነት ከቡድን ነፃነት ቀዳሚነት፤ የሕይወትና የምግብ መብት መከበር፤ ቢያንስ የአንድ ብሄራዊ ቅዋንቅዋ አስፈላጊነት፤ ፍትሃዊ የፖለቲካ አስተዳደር፤ ሁሉን አቀፍ የሆነ ብሔራዊ ውትድርናና የሲቪል አገልግሎት፤ የነጻ ገበያ ኢኮኖሚ፤ በሙሉ ነፃነት የሚንቀሳቀሱ የሲቪክና የፓለቲካ ድርጅቶች፤ እንደዚሁም የመንግሥት ድርጅቶች አሠራር ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነብት መሆን ይኖርበታል።

በሀገራችን ያለው ሥር የሰደደ ችግር በመሠረቱ ጥልቅ ጥናትና ምርምር ይጠይቃል። ሕዝብን በዘር በመከፋፈልና በአንድ ጠባብ ብሄርተኝነት ፖሊሲ ማስተዳደር ችግሩን የበለጠ ያብብሰዋል እንጂ ለዲሞክራሲና ለሀገር ብልጽግና መሠረት አይሆንም። እንደዚሁም ግልጽ ያልሆኑ ፕሮግራሞች፤ ከውጭው ዓለም የተቀዱ አይድኦለጂና ባዶና ፍሬ ቢስ ፕሮፓዳንዳ ለሀገራችን የሚያስገኙት ጥቅም የለም።

ኢትዮጵያዊነት ይኅንኑ በመገንዛብ የሀገራችን ተጨባጭ ሁኔታ ላይ በመመሥረት አሁን ያለው ዘረኛ ሥርዓት ሲወገድ ለችግሮቹ ሀገራዊ መፍትሄ ለማስገኘት ብቃት ባላቸው ምሁራንና ባለሞያዎች አማካኝነት ለሽግግሩና የቀጣዩን ሥርዓት አካሄድ የሚጠቁሙ አማራጮች ላይ የጥናት ጽሁፎች እንዲቀርቡ በ፤ማድረግ ላይ ይገኛል። በዚህም መሠረት ኢትዮጵያዊነት እስከአሁን ሁለት ጥናታዊ ጉባኤዎች አካሂዶአል። በእነዚህ ጉባኤዎችም 12 ምሁራኖች በተለያዩ አርዕስቶች ላይ ጥናታዊና የምርምር ጽሁፎች እየቀረቡ ውይይት ተካሂዶባቸዋል። በ2015 የቀረቡት ጥናቶች አዲስ ሕገ መንግሥትን ፤ አዲስ የኢኮኖሚ ፖሊሲን ፤ የሽግግሩ ዋና ዋና ተሳታፊዎችን መለየትንና የሽግግር አፈፃፀሙ ላይ ያተኮሩ ነበሩ። ዋናዎቹ የጥናት ጽሁፎች በዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ዓውደ ጥናት መጽሄት (International Journal of Ethiopian Studies) ታትመው ወጥተዋል። የመክፈቻ ንግግሮቹም በኢትዮጵያዊነት ድህረ ገጽና (www.ethiopiawin.net) በዩ ትዩብ (youtube) ላይ ይገኛሉ። 3

ሰሞኑን የተጠናቀቀው የ2016 ጥናታዊ ጉባኤ ደግሞ የኢትዮጵያዊነትን ታሪካዊ አመጣጥና በአሁኑ ወቅት ከሚራገበው ጠባብ የማንነት አባዜ የሚገላግለን፤ ብሄራዊ መለያችንና መገለጫችን ሊሆን የሚችልና የሚገባ ብቸኛ አማራጭ መሆኑን በማያሻማ ህኔታ ያረጋገጠ ነው። እንደዚሁም በሶስት አማራጮች ላይ ያተኮረ የመንግሥት አወቃቀር፤ ቀደም ሲል ከነበሩ የመንግሥታት አስተዳደር ዓይነቶች ልንማር ስለምንችለው ደካማና ጠንካራ ጎኖች ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበዋል።

የህወሃት መንግሥት በተደጋጋሚ በተግባር እንደታየው ሕዝቡ የሚያነሳቸው የመብትና የነፃነት ጥያቄዎች የአገዛዙ ማብቂያ እንደሆነ ስለሚገነዘብ እስከ አሁን ለሕዝቡ ጥያቄዎች የሰጠው መልስ ግድያ፤ ማሰርና ማንገላታት ብቻ ሆኖአል። የኢትዮጵያ ሕዝብ ከሐረር እስክ ጎንደር ከጋምቤላ እስከ ወለጋ በማያወላውል መልኩ በቃ በማለት በመላ ሀገሪቱ የክተት ጥሪ እያተስተጋባ ነው። የአምባገነንና የዘረኝነት አገዛዝ ይብቃ ብሎ የፍርሀት ሽባቡን በጣጥሶ በአንድነትና በእምቢተኝነት ገንፍሎ ወጥቶአል። የሕዝቡ የበላይነት ከመንግሥት የሚለገስ ስጦታ ሳይሆን በትግል የሚገኝ የመስዋዕትነት ዉጤት መሆኑን በሚገባ ተረድቶታል።

ወገኖቻችን ምሬታቸውን ለማሰማት ስላማዊ ስለፍ ቢወጡም አምባገነኑና ዘረኛው መንግሥት በአጋዚ ጦሩ አልሞ ተኮአሾች እስክ አሁን በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ሲገድል በሺዎቸ የሚቆጠሩ አቁስሎአል፤ አስሮአል። ስለዚህ፤ ኢትዮጵያዊነት የውድ ወገኖቻችንንና የሕዝባችንን ትግል፤ ብልሀትና ጥንቃቄ በተሞላበት መንግድ እንድንደግፍ እጥብቆ ያሳስባል። አምባገነኑና ዘረኛው መንግሥት መውደቁ አይቀርም። የኛ ተግባር በተቻለን አቅም የሀገራችንና የወገኖቻችን አንድነት እንዳይናጋ መከላከል ሲሆን በአንጻሩ ትግሉን የሚረዱ ጠቃሚ ሀሳቦችንና ለቀጣዩ ሥርዓት ጠንካራ አማራጮችን አጥንቶ ማቅረብና ማመቻቸት ሊሆን ይገባል።

በዚህ አንፃር፤ ኢትዮጵያዊነት የሚከተሉትን ጥሪዎች ያቀርባል፤

1. "የዜጎች ቃል ኪዳን ለዲሞክሪያሲያዊት ኢትዮጵያ" ሰነድና ከፍ ብሎ ከተጠቀሱት ሁለት ጉባኤዎች የተገኙ የጥናት ውጤቶች፤ በሌሎች ድርጅቶች በኩል ከተከናወኑ ተመሳሳይ ጥናቶች ጋር ተዳምሮ ለኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲሰራጭና በዚህ ላይ የተቀነባበረ ብሔራዊ አጀንዳ በጋራ ለመቅረጽ የሚያስችል ሁሉን አቀፍ ውይይት እንዲደረግ፤

2. የፖለቲካልና የሲቪክ ድርጀቶች፤ እንዲሁም ሀገር ወዳድ ወገኖች በሙሉ የግለኝነት አዝማሚያቸውን ትተው "ዛሬ ትብበር ነገ ውድድር" በሚል መፈክር ሥር ትግላቸውን እንዲያቀነባብሩ፤

3. ከሀገር ውጭ የምንገኝ ወገኖች በሀገራችን በህወሃት/ኢህአደግ የሚካሂደውን ግድያ፤ እስራትና መጠን የለሽ የመብት ረገጣ ለምንኖርባቸው ሀገሮች መንግሥታቶች፤ የሕዝብ ተወካዮችና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች በማሳወቅ እርምጃ እንዲውስዱ ቀጣይነት ያለው ያላሰለሰ ጥረት እንድናደርግ፤

4. በሀገር ቤትም ሆነ በውጭ የሚኖሩ ንቅናቄዎች ጠባብና ግለኝነት አመለካክትና ፍላጎቶችን አስወግደው በብሔራዊ አንድነት ዓላማ ሥር እጅ ለእጅ ተያይዘው ሁሉን አቀፍ ሀገር የማዳን ትግሉን እንዲያፋፍሙ፤


4


በተጨማሪም ኢትዮጵያዊነት፤ ለአሜሪካ፤ ለካናዳ፤ ለቻይናና ለአውሮፓ ማህበር፤ የሚከተሉትን መልክቶች ያስተላልፋል፤


1. ሽብርተኝነትን ለመዋጋት በሚል ስበብና የኤኮኖሚ ጥቅም ለማግኘት ሲባል በህወሃት/ኢሀአዴግ በሕዝባችን ላይ የሚፈጸመውን ኢስብዓዊ በደል እያያችሁ እንዳላየ ማለፍና የሕዝቡን ሰቆቃ የሚያባብስ ድጋፍ መስጠታችሁን እንድታቆሙ እንጠይቃለን።

2. በተለይም ሕዝባችንን ለመግደያና ለማፈኛ የሚሆን የጦር ማሣሪያና የኢኮኖሚ ዕርዳታችሁን በአስቸክዋይ ማቆም አለባችሁ። የአፍሪካ ቀንድ ሌላ መንግሥት አልባ ሥርዓት አትሻም። የአንድ መቶ ሚሊዮን ሕዝብ ድምፅ መደመጥ ይኖርበታል።

የተባበረ ክንድ ያሸንፋል

የኢትዮጵያውያን የነፃነት ጩኅት በመላው ዓለም ያስተጋባል

ነፃነት ወዳዱ የኢትዮጵያ ሕዝብ በእርግጠኝነት ያሸንፋል

ይህ የውሳኔ መግለጫ እ ኤ አቆጣጠር ኦገስት 7 ቀን፤ 2016 በተሰበስበው የኢትዮጵያዊነት የዜጎች መብት ማስከበሪያ ጠቅላላ ጉባኤ፤ በታይሰን፣ ቨርጂንያ፤ አሜሪካ የፀደቀ ነው።