Wednesday, July 10, 2013

ናሳ (NASA) በ”ማርስ” ከእግዚአብሔር መልዕክት አገኘ:: (…ምን ይሆን ምስጢሩ?!)

ዘገባ:- “ዘዴይሊ ከረንት - The Daily Current 
ትርጉም:- ዲያቆን : ዳዊት : ብርሃኑ::

“በልዎ ለእግዚአብሔር ግሩም ግብርከ::” (መዝሙረ ዳዊት ፷፭ : ፫)

ብሔራዊ የአየርና ሕዋ ምርምር መስሪያ ቤት “ናሳ” (National Aeronautics and Space Administration) በ”ማርስ” ከእግዚአብሔር የተላከ መልዕክት አገኘ:: “ናሳ” ሰኔ 24, 2005 ዓ.ም. ባወጣው ዘገባ “ኪሪዮሲቲ ሮቨር” (Curiosity Rover) ረቂቅ መልዕክት ከእግዚአብሔር (በታቦት ምሳሌ የተጻፈ) “ማርስ” ላይ በሚገኝ ዋሻ ውስጥ አግኝቷል:: እንደ ጋዜጣዊው መግለጫ ከሆነ ይህ ጽሑፍ የተገኘው በሁለት ግዙፍ /መንትያ/ (የትንሽ ዝሆን ያክል ትልቀት ባለው) ድንጋዮች ላይ ሲሆን: ቦታውም “ኤኦሊስ ሞንስ” (Aeolis Mons) በተባለ ትልቅ ተራራ ላይ ባለ ጥልቅ ዋሻ ውስጥ ነው:: በዚህ የጽላት ቅርጽ ባለው መንትያ ድንጋይ ላይ (ኦሪት ዘጸአት ሙሴ የተቀበለውን አስርቱ ቃላት ያለበትን ጽላት ይመለከቷል:: “ወወሀቦ ፡ ለሙሴ ፡ ሶበ ፡ ፈጸመ ፡ ተናግሮ ፡ ምስሌሁ ፡ በደብረ ፡ ሲና ፡ ክልኤ ፡ ጽላተ ፡ ዘትእዛዝ ፡ ጽላተ ፡ ዘእብን ፡ ጽሑፋት ፡ በአጽባዕት ፡ እግዚአብሔር ።” (ኦሪት ዘፀአት: ፴፩ : ፲፰) - Refer Exodus 31:18) አስርቱ ትዕዛዛት እና በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ሶስት ቁጥር አስራ ስድስት.. በእርሱ የሚያምን የዘላለም ህይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን ወዷል (John 3:16) ያሉት ቃላት በአስራ ሁለት የተለያዩ ቋንቋዎች
(እንግሊዘኛ : ስፓኒሽ : ቻይና : ባስቅ : እና ዕብራይስጥን ጨምሮ) ተጽፎ ተገኝቶበታል:: በሌላኛው መንትያ ድንጋይ ላይ ደግሞ በእንግሊዘኛ ቋንቋ “I am Real” እውነት ነኝ /ህልው ውእቱ/ “ያለሁ / ህልው ነኝ::” የሚል ተጽፎበት ተገኝቷል:: እንደ ታላላቅ ሳይንቲስቶች (በዘርፉ ላይ ጥልቅ ምርምር ባካሄዱት) ምስክርነት ይህ ግኝት የክርስትናን ቀዳማዊነትና እውነተኛ መሰረትነት አረጋግጧል::

 “ይህ ድንቅ ነው!” በማለት ምስክርነታቸውን የሰጡት ደግሞ አውስትራሊያዊው ተመራማሪና በ”ናሳ” የማርስ ምርምር መርሐግብር ላይ የሚሰሩት “ሲምስ ኮቪንግተን” (Syms Covington) ናቸው:: “ወደዋሻው ውስጥ የገባነው ውሃ ለመፈለግ / መኖሩን ለማረጋገጥ ነበር:: በእርሱ ፈንታ ግን የእግዚአብሔርን መኖር በማስረጃ አረጋግጠናል:: ማለቴ እነዚህ ጽላቶች (tablets) እንዴት እዚያ ተገኙ? አንድ ነገር ልነግራችሁ እችላለሉ:- በ’ናሳ’ የቁጥጥር ክፍል ውስጥ አሁን ማንም በመላምት የሚያምን የለም:: ያየነው አፍ የሚያስከፍት እጅግ አስገራሚ ነገር ነው::”


የ”ናሳ”ው “ኪሪዮሲቲ ሮቨር” (Curiosity Rover) ማርስ ላይ የደረሰችው ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር ላይ ነው:: ተልዕኮውም የአየር ጸባዩ እና የመሬት አቀማመጡ ለኑሮ የሚመች መሆን አለመሆኑን ለማጥናት ነው:: እስካሁን ድረስም ጥንታዊ የባሕር ንጣፍ እና ሌሎች ኬሚካሎችን በማግኘት ማርስ በቀድሞው ዘመን ለመኖር ምቹ አንደነበር በማረጋገጥ ተልዕኮው የተሳካ ነው:: ቢሆንም ይህ ጽላት (“ሰላም እና ፍቅር - ያሕዌ” የሚል ምልክት/ እንደ ማኅተም ያለበት ነው:: 

ያሕዌ - ማለት ያለና የሚኖር ማለት ነው::) የ”ሮቨሩ” ታላቅ ግኝት ሲሆን በሳይንሳዊ ምርምር ውስጥም እጅግ ጠቃሚና ታሪካዊ መሆኑን ያመላክታል:: “ሰዎች ስለዚህ ነገር ሲሰሙ በማህበረሰባችን ውስጥ ለውጥ እንዲመጣ ግፊት ያደርጋሉ” የሚሉት በጆርጅ ታውን ዮኒቨርሲቲ (Georgetown University) የፖለቲካ ሳይንቲስት “ዲሞክራሲ ለመንፈሳዊ ስርዓት (ካህናት በእግዚአብሔር ስም የሚያስተዳድሩበት ስልጣን) መንገድ መልቀቅ አለበት:: ብዙ አብያተ ክርስቲያናት ሊታነጹ በየትምህርት ቤቱ ጸሎት እንደጥንቱ እንዲደረግ ማበረታታት አለብን:: በጥቂት ወራት ውስጥ ደግሞ ውርጃና የመሳሰሉት ሕገወጥ ስርዓቶች መሆናቸው ይረጋገጣል::” ብለዋል::


“ካለው የተጽዕኖ አቅም ይልቅ ይህ መሬትን የሚያናውጽ ግኝት ምንም አይነት ለውጥ ላያመጣ ይችላል::” በማለት ኮቪንግተን ያላቸውን ፍራቻም ይገልጻሉ:: “እንደ እድል ሆኖ ዋናው የመገናኛ ዘዴ (ሚዲያ) ጸረ-ክርስቲያናዊ ስለሆነ ይህንን ታሪክ ላያቀርበው ይችላል::” የሚሉት ኮቪንግተን “እግዚአብሔር ግን እውነት አንደሆነ በሁሉም ቦታ እንዳለና ህያው እንደሆነ ማስረጃ አለን:: ይህንን እውነተኛ ታሪክ ግኝት ሁሉም ሊያውቅ / ሊያገኝ ይገባል::” ብለዋል::

የዚህ ግኝት መጨረሻው ...…ምን ይሆን ምስጢሩ?!!!

No comments:

Post a Comment