Monday, March 11, 2013

ጋዜጠኛ ፋሲል የኔአለም በኖርዌይ


አንጋፋው የኢሳት ጋዚጠኛ ፋሲል የኔአለም በትናትናው እለት march 09,2013 በኖርዌይ ኦስሎ የስራ ጉብኝት ባደረገበት ጊዜ በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያኖች የኢሳትን ደጋፊነታቸውንና አጋርነታቸውን ለመግለጽ በኢትዩጵያ ኮሚኒቲ ተሰባስበው የእራት ግብዣ አድርገውለታል።


በዝግጅቱ ላይ በኖርዌይ የሚኖሩ በርከት ያሉ ኢትዮጵያዊያኖች ከተለያዮ ስፍራ በመገኘት ስለ ኢሳት አመሰራረትና በሃገራችን ውስጥ ስላለው የስብአዊ መብት ጥሰት ከሐገር ቤት ከሚደርሳቸው ዘገባ በመነሳት ስላለው ሁኔታና እንዲሁም የተለያዮ እርእሶችን በማንሳት በስፋት ሲወያዮ አምሽተዋል ።

በመጀመሪያም በኖርዌይ የኢትይዮጵያ ኮሚኒቲ ተወካይ የሆኑት አቶ ቢትወደድ ጸጋዬ የእንኳን ደህና መጣህ ንግግርና በፌብርዋሪ10.2013 በተሳካ ሁኔታ ለተጠናቀቀው የኢሳት ገቢ ማሰባሰቢያ በማውሳት ኢሳት ለኢትዮጵያኖች አይንና ጆሮ እንደሆነና መደገፍ የሚገባው ድርጅት እንደሆነ የሚገልጽ የድጋፍ ንግግር አድርገው የኖርዌይ ኢትዮጵያኖች ለኢሳት ያላቸውን ድጋፍና በአንድ እግሩ ለማቆም ከሚንቀሳቀሱ ድርጅቶችም ሆነ ግለሰቦች ጋር ተባብሮ ለመስራት ያላቸውን አጋርነት በመግለጽ በህዝቡ ስም ዝግጅቱን ከፍተዋል።

ጋዜጠኛ ፋሲልም ከተለያዮ ታዳሚዎች የቀረቡለትን ጥያቄዎችንም በተገቢው ሁኔታ በስፋት በማብራራት ለታዳሚዎቹ ሲገልጽ አምሽቷል በተለይ ሃገር ቤት ሆነው ስልክ የሚደውልሏቸውን ወጣቶች ያላቸውን የፖለቲካ ብቃትና በእድሜአቸውም ማነስ እያነጻጽረ ምን ያህል ወጣቱ በፖለቲካ ብቃት መጎልበቱን በማድነቅ ለታዳሚዎቹ ሲያጫውታቸው አምሽቷል።

በመጨረሻም ጋዜጠኛ ፋሲል የኔአለም ታዳሚዎችን በእርሱና በኢሳት የስራ ባልደረቦቹ ስም አመስግኖ ወደ ተዘጋጀለት ማረፌያ በክብር ተሸኝቷል። ከዛም በጠዋት ወደ ሚኖርበት ሆላንድ አምስተርዳም ከተማ አቅንቷል።


ጋዚጠኛ ፋሲል የኔአለም በኢትዮጵያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሞት ፍርድ እንደ ተላለፈበት ይታወሳል

http://www.rnw.nl/africa/article/exiled-ethiopian-journalist-convicted-terrorism



እስክንድር አሰፋ ከኖርዌይ

ማርች 10.2013

 

No comments:

Post a Comment