Tuesday, March 5, 2013

በውጪ አገር ያሉትን አባቶች ያጋልጣል የተባለ ትንሽ መጽሐፍ ተሰራጨ


  • ቤተ ክህነቱ ይህንን ያደረገው ዕርቁ የፈረሰው በውጪዎቹ ችግር መሆኑን ለማጠየቅ ነው፤
  • የደጀ ሰላም ምንጮች “ቤተ ክህነታዊ ሐረካት” ብለውታል። 

(ደጀ ሰላም፤ የካቲት 26/2005 ዓ.ም፤ ማርች 5/2013/ PDF)፦ በስደት የሚገኙነትን አራተኛው ፓትርያርክ ጨምሮ በውጪ አገር ያሉ አባቶችን ስሕተት፣ ጥፋትና ዕርቀ ሰላሙን ማፍረስ የሚያትት እንዲሁም ፓትርያርኩ ከሥልጣን የወረዱት ተገደው ሳይሆን በራሳቸው ፈቃድ መሆኑን የሚያትት ባለ 52 ገጽ አነስተኛ መጽሐፍ ታትሞ በመሰራጨት ላይ ነው።


ይኸው በአቡነ ማቲያስ ዕለተ ሲመት ጀምሮ መሰራጨት የጀመረው መጽሐፍ በብዙዎች አባባል የቤተ ክህነቱ “ጂሐዳዊ ሐረካት” የተሰኘ ሲሆን አዲስ ተሿሚው ፓትርያርክ ይቀጥላል ሲሉ ተስፋ ከሰጡት የዕርቅ ሒደት ተቃራኒ ሆኖ ተገኝቷል። በኢትዮጵያ ቴሌቪዥንም “ዶኩመንታሪ” ፊልም እንዲሰራበት ኮሚሽን ተከፍሎበታል በሚባለው በዚህ ርዕሰ ጉዳይ ዕርቁን በጉጉት ይጠብቅ የነበረውን ምእመን ለማሳመን ረብጣ ብር እየፈሰሰ ነው።  

ይህንን አጭር መጽሐፍ/ ዶኩመንት ለመመልከት ይህንን ይጫኑ።

ቸር ወሬ ያሰማን፣ አሜን

No comments:

Post a Comment