Wednesday, March 20, 2013

ዲኢህዴን አቶ ሃይማርያም መለስን በሊቀመንበርነት መርጧል


አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 11 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢህዴን) አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝን የንቅናቄው ሊቀመንበር አደርጎ መረጠ።
አቶ ሽፈራው ሽጉጤን ደግሞ  በምክትል  ሊቀመንበርነት መርጧል ።
ጉባኤው ዛሬ ካካሄደው የንቅናቄው ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ምርጫ  ጋርም ሰባት የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ አባላትን ጨምሮ 15 የንቅናቄው ስራ አስፈፃሚ አባላትን መርጧል ።
በዚህም መሰረት አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝንና አቶ ሽፈራው ሽጉጤን ጨምሮ አቶ ሬድዋን ሁሴን ፣ አቶ መኩሪያ ሀይሌ ፣ አቶ ሲራጅ ፈጌሳ ፣ ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያም ፣ አቶ ዓለማየሁ አሰፋ ፣ አቶ ደሴ ዳልኬና አቶ ተስፋዬ በልጂጌ የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ተደርገው ተመርጠዋል ።
እነዚህ  የኢህአዴግ  ስራ አስፈፃሚ  አባላትን ለሚያካትተው የደኢህዴን ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ደግሞ አቶ ተክለወልድ አጥናፉ  ፣ አቶ መለሰ ዓለሙ ፣ ወይዘሮ ሙፍሪያት ካሚል ፣ አቶ ታገሰ ጫፎ ፣ አቶ ደበበ አበራና አቶ ሳኒ ረዲ በአባልነት ተመርጠዋል ።
በጉባኤው በአጠቃላይ 250 አባላትን በባህር ዳር ከተማ በሚካሄደው የኢህአዴግ ምክር ቤት  መደበኛ  ጉባኤ ላይ እንዲሳተፉ የተመረጡ ሲሆን ፥  ከነዚህ መካከልም 45ቱ የምክር ቤቱ አባላት ናቸው ።

No comments:

Post a Comment