Sunday, February 2, 2014

የዲሞክራሲ ለውጥ በኢትዮጵ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌ የሴቶች እና የወጣት ክፍል ሲያስመርጥ ዋለ

 በJan 31,2014 የዲሞክራሲ ለውጥ በኢትዮጵ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ  የሴቶችና የወጣት ክፍልን በማጠናከር ለቀጣይ ሁለት አመታት ድርጅቱን የሚያገለግሉ ኮሚቴዎችን የድርጅት ክፍል ኃላፊው አዋቀሩ። በእለቱ የድርጅቱ ወጣት አባላትና የቀድሞው ኮሚቴዎች በስብሰባው ላይ በመገኘት ለምርጫው መሳካት የነቃ ተሳትፎ  አድርገዋል።

ያለፉት የወጣቶች ክፍልና የሴቶች ክፍል ኮሚቴዎች ለአዲስ ተመራጮች የስራ ልምዳቸውን በማጋራት በቀጣይም ሐገራቸውን ከወራሪው የወያኔ ስርአት ነፃ ለማውጣት ወጣቱ ትውልድ በውጪም ሆነ በሐገር ውስጥ ያለውን እንቅስቃሴ የመምራት ሐላፊነት ያለበት በመሆኑ እጅ ለእጅ በመያያዝ በጋራ ለመስራት መክረዋል።

ለመጪው ሁለት አመታት እንዲያገለግሉ የተመረጡት ኮሚቴዎችም የተሰጣቸውን ሐላፊነት ለመወጣት ቃል በመግባት የእለቱ ምርጫ በኖርዌ ሰአት አቆጣጠር 17፡00 ሰአት አጠናቀዋል ።







እስክንድር አሰፋ / ኖርዌ

No comments:

Post a Comment