Wednesday, August 31, 2016

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለወቅቱ ሁኔታ

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር ኢሕአዴግ ሲነሣ ከነበረበት ሁኔታ አሁን ያለው ነባራዊ ሁኔታ የተለወጠ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ አስታውቀዋል፡፡


የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር የኢሕአዴግን ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴና የማዕከላዊ ምክር ቤቱን ጉባዔ ተከትሎ ለመንግሥታቸው መገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ “ኢሕአዴግ ግዙፉን የደርግ ሥርዓት በሚደመስስበት ጊዜ ካስቀመጣቸው እሤቶች መካከል እራስን ለሕዝብ የመስጠትና ለሕዝብ የመኖር ጉዳይ ወሣኝ ጉዳይ ነው ተብሎ የተያዘ ነው፤ ነገር ግን ነባራዊ ሁኔታው ተቀይሯል” ብለዋል፡፡


ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም “ነባራዊ ሁኔታው በተቀየረበት ሁኔታ አመራሩ የመንግሥትን ሥልጣን የሚያይበትና በተግባርም የሚፈፅምበት ሁኔታ በሚገባ ካልተቀየረ አሁን ባለንበት ደረጃ የጉዟችን እንቅፋትና መሠናክል የበዛበት ጉዞ ይሆናል” ብለዋል፡፡


ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡


http://amharic.voanews.com/pp/3487227/ppt0.html

No comments:

Post a Comment