Wednesday, August 31, 2016

የመኢአድ ጋዜጣዊ መግለጫ

የድርጅቱ ባለሥልጣናት በንባብ ባሰሙት ባለ-ሰባት ነጥብ የአቋም መግለጫ ያቀረቧቸዉ ጥያቄዎች ባስቸኳይ ካልተሟሉ ፓርቲያቸዉ ከሕዝብ ጎን ቆሞ በሰላማዊ መንገድ እንደሚታገል አስጠንቅቀዋል።
የመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ትናንት በሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ መንግሥት ፀጥታ አስከባሪዎች ለተቃዉሞ አደበባባይ በወጡ ሠላማዊ ሰልፈኞች ላይ የወሰዱትን የሐይል እርምጃ የግፍ ጭፍጨፋ በማለት አወገዘዉ።የኢትዮጵያ መንግሥት ሕገ-ወጥ በሚል ሽፋን የሠላማዊ ዜጎችን ቤት እያፈረሰ ነዋሪዎችን ማፈናቀሉን እንዲያቆምም ድርጅቱ ጠይቋል።የድርጅቱ ባለሥልጣናት በንባብ ባሰሙት ባለ-ሰባት ነጥብ የአቋም መግለጫ ያቀረቧቸዉ ጥያቄዎች ባስቸኳይ ካልተሟሉ ፓርቲያቸዉ ከሕዝብ ጎን ቆሞ በሰላማዊ መንገድ እንደሚታገል አስጠንቅቀዋል።
http://www.dw.com/am/የመኢአድ-ጋዜጣዊ-መግለጫ/a-19513038


ጌታቸዉ ተድላ ሐይለ ጊዮርጊስ
ነጋሽ መሐመድ
አዜብ ታደሰ


 Audios and videos on the topic

No comments:

Post a Comment