Sunday, March 9, 2014

Female activists arrested following anti government protest in Ethiopia

Semaywi Party women members and supporters arrested following the women protest against injustice during women's great run in Addis Ababa today March 09, 2014.



በሴቶች ነፃነት ቀን በሚከበርበት ወቅት የኢህአዲግ አምባገነን ስርዓት ተቃውሞ አሰምታችኋል በሚል የሰማያዊ ሴቶችንና አብረዋቸው የነበሩትን ሁሉ አስሯል፡፡ እጅግ አስገራሚው ክስተት ደግሞ የኢህአዲግ ሴቶች ሊግ ፣ የሴቶች ፎረም(ኢህአዲግ የሚያዘው) እና አገዛዙ ያስተባበራቸው በርካታ ማህበራት በነፃነት ሩጫውን ያሻቸውን እያሉ ሲያጠናቅቁ ነፃነትን እንፈልጋለን ፣ ፍትህ ናፈቀን ፣ የህሊና እስረኞች ይፈቱ ፣ ኑሮ መረረ ፣ ሴቶችን በማስፈራራት አምስት ለአንድ መጠርነፍ ይቁም እና የመሳሰሉትን የተቃውሞ ድምፅ ያሰሙ የነበሩ ሰላማዊ ታጋዮች መታሰራቸው ነበር፡፡ በዚህም የኢህአዲግ ስርዓት በሴቶች ቀን የሴቶችን መብት እንደማያከብር በይፋ አረጋግጧል ፤ ሀሳባቸውን በነፃነት መግለፃቸው ወንጀል ሆኖ አፍኗቸውል፡፡ 

ከስር የምታዩት ምስሎች የኢህአዲግ ደህንነቶችና ፖሊሶች ሴቶችን እየለቀሙ ሲያፍሱና ሲይዙ ያሳያል

ድል ለኢትዮጵያ ሴቶች 
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!

Semayawi Party- Ethiopia's photo.

No comments:

Post a Comment