Wednesday, October 16, 2013

ዓረና ትግራይንና አንድነት ፓርቲን በመደገፋቸው የከተማዋን ኗሪ ቀስቅሳችሃል በሚል በጽጥታ ሃይሎች የተያዙ ወጣቶች ያሉበት አድራሻ እስካሁን ድረስ አልታወቀም

ወጣቶቹ የፈጸሙት ምንም ዓይነት ወንጀል ባይኖርም ዓረና ትግራይንና አንድነት ፓርቲን በመደገፋቸው የከተማዋን ኗሪ ቀስቅሳችሃል በሚል መስከረማ 27,2006 ዓ/ም በስርዓቱ የጸጥታ ሃይሎች ታፍነው የተወሰዱ ዜጎች እስካሁን ድረስ ያሉበት አድራሻ በትክክል ካለመታወቁም በላይ የቀረበባቸው ክስ የለም፣ ከታፈኑት ዜጎች መካከል መምህር ስዓረ ፤ እንጂነር ነጋሲ ገብሩ፤ አቶ አንገሶም ተስፋይና ወ/ሮ ቅዱሳን ኣብርሃ (ነባር ታጋይ) ይገኙበታል፣ ይህ በእንዲህ እያለ በሽረ-እንዳስላሰ ከተማ ቀበሌ 03 ከጀርመን የህክምና ማEከል አከባቢ ዓረና ትግራይ አዲስ መስከረም 24,2006 ዓ/ም ጽ/ቤት የከፈተ ሲሆን በስነስርዓቱ በርካታ የከተማዋ ኗሪ ህዝብ ተገኝቶ እንካን ደህና መጣችሁ በማለት በጽ/ቤት በከፍተኛ ክብር የባንዴራ ማውጣት ስነስርዓት ተሳትፋል፣ በመክፈቻው ስነስርዓት አምባገነኑ የIህአዴግ መንግስት ይውረድ ! ፤ ሙስና ይወገድ! ህጋዊና ዴሞካሲያዊ ስርዓት ይመስረት! የሚሉ ወቅታዊ መፈክሮች በጽ/ቤት በግልጽ ይታዩ ነበር::

No comments:

Post a Comment