Saturday, December 28, 2013

ፍትህ የተጠማች ብላቴና



በአንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ወቅት ታዳጊዋ ፍትህን ጠየቀች (ከፍኖተ ነጻነት የተወሰደ)

«ይህች ህጻን አማራም፣ኦሮሞም፣ጉራጌም፣ትግሬም ፣ሙስሊም፣ክርስቲያን ፣የኢህአዴግ ተቃዋሚ ወይም ደጋፊ ፣ሽፍታ አይደለችም፡፡ለሁሉም ያልደረሰች ህጻን ብቻ ናት፡፡ሁላችንንም የምትጠይቀን ፍትህ ብቻ ነው፡፡አባቷን ገድለው እጇን በጥይት ቆርጠዋል፡፡ምናልባት ሳድግ መምህር የመሆን ህልም አለኝ ብላኛለች፡፡ማን ነው ለዚህ ህልሟ የሚያደርሳት ?ወዳጄ ነገ ከነገ ወዲያ በአዲስ አበባ በአንድ ቦታ ሳንቲም ትሎት ወይም ትለን ይሆናል፡፡እውን ህመሟ ይሰማናል?ይሰማቸዋል?» ሲል ነበር የአንድነት ጥቅላላ ጉባኤ ተካፋይ አባቷን እንዲሁም እጆቿን ያጣችዉን ታዳጊ ወጣት ሲያስተዋወቅ የተነገሩት።

አባቷን በጥይት የተነጠቀችውና እጇን የተቆረጠችው ታዳጊ በጠቅላላ ጉባኤው በቀረበበችበት ወቅትም ፣ አባላቱ በእንባ ታጥበዋል፣ቁጭት ውስጣቸውን አንገብግቦት ‹‹ፍትህ፣ፍትህ፣ፍትህ» በማለት ጩኅታቸውን አሰምተዋል።

አባቷ ለበርካታ አመታት የኢሕአዴግ /ብሃዴን አባል የነበሩ፣ መዋጮ የሚያዋጡ ሰው ነበሩ።ሰባት ልጆች የነበሯቸው ሲሆን በዚህ ሁኔታ ሕይወታቸው ማለፉ የአገዛዙን ምንነት ብዉ አደርጎ ያጎላ ነዉ።

ቪዲዮዉን ይመልከቱና ይፍረዱ !





No comments:

Post a Comment