Sunday, December 2, 2012

Destroying Ethiopia’s History for the Sake of Development


It was in 1896 that Ethiopian forces led by Emperor Menelik II had defeated an Italian army with better contemporary military technology at the Battle of Adwa [1]. Subsequently, the victorious Emperor had brought in a range of technologies including railway to transform his country. For his triumph at Adwa and for his endeavor to change Ethiopia in his own ways, a statue in his honor was erected at the center of Addis Ababa called Arada.
Almost forty years later, in 1935, the Italians launched a new but a prearranged military campaign [3] endorsed by their then belligerent leaders. The Italians managed to have a brief military occupation of Ethiopia but faced a staunch resistance from Ethiopians.
Pope Abune Petros, who was among the first Popes of Ethiopian Orthodox Church, was the leading figure of the resistance in Ethiopia. The Italians never liked what he was doing as a patriot and tried to stop him. He was forced to appear [4]before General Rodolfo Graziani to submit and declare the Ethiopian patriots as bandits. He refused to comply with their demand and condemned the aggressors instead. He asked Ethiopians to struggle for their freedom. Finally, the Italians executed him in public. As it was done with Emperor Menelik II, a statue of Abune Petros was built at the center of Addis Ababa as reminiscent of his unwavering stand for his country.
However, unconfirmed reports are circulating online that the two iconic statues found on an historical thoroughfare might get wrecked due to an Addid Ababa rail tunnel construction project. The reports have not been received well by some netizens.
Daniel Kiberet, a blogger who usually write on culture, history and spirituality of Ethiopia, asks [5] [amh]:
ይህ የባቡር መሥመር የአቡነ ጴጥሮስንና የዐፄ ምኒሊክን ሐውልት እንዲነሡ ያደርጋል?
ለዚህ ጥያቄ ምላሹ ‹አዎን› ከሆነ ስለ ባቡሩ የሚኖረን ግምት ይለያል፡፡ ኢትዮጵያን እናሳድጋለን ስንል ያሳደጓትን እየዘነጋንና መታሰቢያቸውን እያፈረስን መሆን የለበትም፡፡ ‹በማን ላይ ቆመሽ እግዜርን ታሚያለሽ› አለ ያገሬ ሰው፡፡ የምናመጣው አዲስ ነገር ባለን ላይ የሚጨመር እንጂ ያለንን የሚያጠፋ መሆን የለበትም፡፡ መኪና ያስፈልገናል፣ ግን እግር የሚቆርጥ መሆን የለበትም፡፡ ወደድንም ጠላንም ይህች ሀገር የታሪክና የቅርስ ሀገር ናት፡፡ ይህ ታሪኳና ቅርሷ ደግሞ የህልውናዋም ምንጭና መሰንበቻም ጭምር ነው፡፡ ይህን ታሪክና ቅርስ እያጠፉና እያበላሹ የሚመጣ ለውጥ አንገት ቆርጦ ፀጉርን እንደማስተካከል ነው የሚቆጠረው፡፡ እናም የሚመለከታቸው ሁሉ ወደ ርምጃ ከመግባታቸው በፊት ሦስት ጊዜ ሊያስቡ ይገባል፡፡ መቼም የመጀመርያውን ባቡር ያስገቡትን የዐፄ ምኒሊክን ሐውልት አፍርሶ ባቡር እናስገባ ማለት የታሪክ ምጸት ነው፡፡ ለነጻነት የተሠውትን የአቡነ ጴጥሮስ ሐውልት ነቅሎ በባቡር ላይ በነጻነት ለመሄድ መከጀል ግፍ መሥራት ነው የሚሆነው፡፡”
Will the Addis Ababa rail lines construction destroy the statues of Emperor Menelik II & martybishop Abune Petros?
If the answer to this question is yes, our stance for the rail lines construction would be different! Our development should not come at the expense of the statues of forefathers of Ethiopia who have given their life for the country! There is a saying which says “Are you gossiping God while you give your weight for the soil!” What we put in for development should reflect on what we already have, it should not destroy what we have. We might need vehicles but the vehicles should not cut off our feet. Whether we like it or not Ethiopia is a country with rich history and heritage and these are foundations for our survival and continuation. So constructing rail lines at the cost of Ethiopia’s iconic figures is like going to a barber shop for hair cut after amputating one’s head! The project group should think thrice before they decide to demolish these statutes. Destroying a figure of a man who had built the first railway in Ethiopia a century ago to construct rail lines is a complete sarcasm! Demolishing the statute of a man who had given his life for freedom of his country and wishing to commute freely on the train is an indulgence.

Raw Video Footage: Government brutality in Ethiopia (መታወቅ ያለበት ጭካኔ)


Former tribal rebels who became government 21 years ago in Ethiopia keep exercising Human Rights abuse. Ethiopian Muslims are the latest victims of the racist tribal regime of Ethiopia. The video footage
 shows a brutal attack against Ethiopian Muslims who rejected and protested peacefully against government interference in their religious affairs.

Meanwhile Ethiopia became a member of UN Human Rights council, while UN knows Ethiopia commits gross human rights violations.

የአዜብ-በረከት የተንኮል እቅድ


መለስ ዜናዊ የስልጣን እድሚያቸውን ለማራዘም ከተጠቀሙባቸው ዘዴዎች አንዱና ዋናው “የትግራይ ህዝብ የሥርዓቱ ልዩ
ተጠቃሚ”እንደሆነ አድረገውበካድሬዎቻችው በኩል ያለመሰልቸት የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ማካሄድ ነበር። ይህ ዘዴ የትግራይ ህዝብ
ተጠቃሚ፤ የኢትዮጲያ ህዝብ ግን የበይ ተመልካች ሆኖ እንዲሰማውአድርጎታል። አቶ መለስ “ነፃሚድያ”ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚቻልሁኔታ ስላጠፉትና የኢትዮጵያ ህዝብም የሳቸውየፕሮፓጋንዳ ሰለባ ስላደረጉት እሳቸውየሚናገሩት እና የሚያወሩት እውነት ይሁን ውሸትለማወቅ ይቸገራል። ያ ውሸት ተደጋግሞ ሲነገረውውሸቱን እውነት ነው ብሎ ይቀበለዋል። አቶ መለስ ኢኮኖሚህ 11 በመቶ አድጓል እያሉነጋ ጠባ ሲወተውቱት፣ ከአመት ወደ አመት ኑሮው እየከፋ፣ ጉልበቱ በረሀብ እየደከመ የሄደው ወገን ውሸቱን እውነት አድርጎ ከመቀበልውጪሌላ አማራጭየለCም።

መለስ የትግራይ ህዝብ አጋዥ አጣ እንጂ በምን አይን እንደሚያያቸውጠንቅቀውያውቃሉ። መለስ እና ኢትዮጵያ እሳትና ጭድ
መሆናቸው ጎልቶ የወጣው በተለይ የኢትዮ-ኤርትራን ጦርነት አክሽፈው፣ የኢትዮጵያ መሬቶችን ለኤርትራ አሳልፈውለመስጠት ባለ
አምስት ነጥብ የሰላም እቅድ የሚል የማጭበርበርያ እቅድ ነድፈው እሱን ለመተግበር ደፋ ቀና ሲሉ በነበረበት ወቅት ማለት ነው!
ቀጥሎም ከመተማ እስከ ጋምቤላ ያለውን እጅግ ለም መሬት ያላንዳች ሀፍረት ለሱዳን እጅ መንሻ ሲያደርጉ፣ ሰውየው ኢትዮጵያን
በሁሉ መንገድ ለማዳከም ቆርጠው የተነሱ እንደሆኑ ታወቀ። ባለፈው አመትም ቢሆን የሻቢያ ሰራዊት በተደጋጋሚ የኢትዮጵያን ድንበርጥሶ፣ በሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አስሮ፣ ያገሬውን የቀንድ ከብቶች፣ በጎችና ፍየሎች እንደልቡ ዘርፎ ሲወስድ፣ መለስ “ሻቢያ ግልጽ ጦርነትእስካልከፈተብን ድረስ፣ በትንንሽ ትንኮሳዎች ተታለን ዋናውጠላታችን የሆነውን “ድህነትን” ከመዋጋት ወደኋላ አንልም” ሲሉ በኢትዮጵያህዝብና ሀገራዊ ሉዓላዊነት ሲያሾፉ ተስተውለዋል።

መለስ ከክልሎች ሁሉ የሚፈሩት እና ጥብቅ ቁጥጥር እንዲደረግለት የሚሹ ቢኖር የትግራይን ክልል ነው። የትግራይ ህዝብ አመፅ ማለትበሰራዊቱ ውስጥ ያለው ወታደርም አመፀ ማለት ነው። ያ ደግሞ የመለስ የስልጣን እድሜ ያሳጥረዋል። ያ አደገኛ ሁኔታ እንዳይከሰትነበር አቶ መለስ ቴዎድሮስ ሐጎስን የክልሉ የበላይ ጠባቂ ያደረጉት። ኤርትራዊውቴዎድሮስ ሐጎስ ከፊሎቹ ወንድሞቹ የሻብያ ተዋጊዎችስለነበሩ፣ ኤርትራ በኢትዮጵያ ላይ ጦርነት ስትከፈት እና መቀሌ የሚገኘውየአይደር የህፃናት ት/ቤትን በቦምብ ሲደብደብ፣ ቁጣውንበሰልፍ የገለፀውየመቀሌ ነዋሪ ህዝብ ከጠየቃቸውጥያቄዎች አንዱ “ቴዎድሮስ ሐጎስን” እንዲባረርለት ነበር። አቶ መለስ ደግሞ እራሱአስጊ ሁኔታ ውስጥ ቢኖርም፣ ፈራ-ተባ ከማለት ውጪ፣ ከኤርትራ ጋር የወገነውን ጠ/ሚኒስቴር ደፍሮ ከስልጣን ሊያባርር የሚችልየህወሓት ኃይል ስላልነበር፣ ቴዎድሮስ ሐጎስን ከማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት አውጥቶ ወደ ኃያሉና ታማኙ የፖሊት ቢሮ አባል አድርጎሾመው። ያቺን የመቀሌ ህዝብ ክስ ለመበቀል ነበር ቴዎድሮስ ሐጎስም በምርጫ97 ጊዜ“ትግሬ ወደ መቀሌ፣ ዕቃ ወደ ቀበሌ” የምትልመርዝ በቅንጅት ስም አዲስ አባባ ሆኖ የረጫት። የኢትዮጵያ ህዝብሙሉ ድጋፍ የነበረውቅንጅት ለዘር ግጭት ትንኮሳ የተበተነችውንመርዝ ተጠያቂው ቅንጅት እንዳልሆነ በሚድያ ወጥቶ ለኢትዮጵያ ህዝብ ለመግለጽ ተደጋጋሚጥያቄ ቢያቀርብምሚዲያውንየተቆጣጠረውበረከት ስምኦን ግን የቅንጅትን ጥያቄ ሊያስተናግድ ቀርቶ አመራሩን እንዳለ በጅምላ ዘብጥያ እንዳወረዳቸውየትናንቱትውስታ ነው።

ዛሬ መለስ የሉም። ያሉት የአቶ መለስ ባለሟሎች ናቸው። በረከት ስምኦን፣ ሳሞራ ዮኑስ፣ ብርሃነ ገ/ክርስቶስ እና ሌሎች የኤርትራ ዝርያያላቸውሰዎች ዋናውን የስልጣን ቁልፍ ከወ/ሮ አዜብ መስፍን ጋር በመሆን አቶ ሀ/ማርያም ደሳለኝን አንደ ጋሪ ፈረስ ከፊት አስቀድመውእየተጓዙ ይገኛሉ። ፍርሃት እናጭንቀት የሞላበት ጉዞ እንደሆነ ግልጽ ነው። “ያለን አማራጭመለስ ሲጠቀምበት የነበረውን ስልትመጠቀም አለብን” እንደሚሉ ልዩ ትምህርትን አይጠይቅም። አንደኛና ዋነኛውደግሞ የትግራይ ህዝብ ከቀሪውወገኑ ጋር እንዳያብርአሁንም ተነጥሎ የሚመታበት መንገድ መዘየድ የግድ ይላል። ይህን ዘዴ ተግባራዊ ለማድረግ የተመደበችው ደግሞ አዜብ ሆናለች።

         “መለስ ትግራይን በኢንዱስትሪ ለማልማት የ5 አመት እቅድ ነድፎ ነበር” - አዜብ መስፍን

አዜብ ኢህአዴግ ወይም ራስዋ በምትቆጣጠረውቴሌቭዥን ሰሙኑን ታይታ ነበር። ጋዜጠኛዋን ያነጋገረቻች ኤፈርት ቢሮውስጥ ቢሆንም፣
አዜብ ግን አሁንም ሀዘን ላይ የተቀመጠች እንደሆነች ተመልካች እንዲያውቅላት የምትሻ ትመስላለች። ድምጽዋ በልቅሶ የጎረነነ
ታስመስለዋለች። “መለስ ትግራይን በኢንዱስትሪ ለማበልጸግ የአምስት አመት እቅድ ጽፎ ነበር!” አለች አዜብ በጎረነነ ድምጽ።
አሃ!ጨዋታ እዚህ ላይ ተጀመረ።

መለስ እሱ ራሱ አልፎ አልፎ ሲናገር እንደተደመጠው ወደ ክልል ወርዶ ጣልቃ ልግባ እንኳ ቢል ጊዜ እና አቅሙእንደሌለው፣ እሱ
የተወጠረው፣ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ጉዳዮች፣ በአፍሪቃ ቀንድ ፖለቲካ (ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኬንያ ወዘተ) ከዛም አልፎበአፍሪቃናበጥቂቶችና በበለፀጉ የዓለም መሪዎች ስብሰባ (G-8 እና G-20) ላይ እየተገኘ በንቃት መሳተፍን እንደሆነ ደጋግሞ ይገልጽ ነበር።

ታድያ ዛሬ ወ/ሮ አዜብ ከነበረከት ስምኦን ጋር ሆነውየጠነሰስዋትን ተንኮል ይዘውወደሚድያ በመቅረብ መለስ ትግራይን የኢንዲስትሪማእከል ለማደረግ መጽሀፍ ጽፏል ብለው አረፉት። መለስ ለትግራይ ልዩ የእንዲስትሪ ራእይ ቢኖራቸው ምነው 21 አመት ሙሉ ስልጣንላይ በነበሩበት ጊዜ አልተገለፀላቸውም? ይቺ ራእይ የአዜብ እና የበረከት “ትግራይን የማጥመድ ራእይ” እንጂ፣ እንደተባለው የልማትራእይ ሊሆን ፈጽሞ አይችልም። ደፋርዋ አዜብ አክላም “የኔ ኃላፊነት የመለስን ራእይ እውን ማድረግ ነው”ካለች በኋላ የEFFORT(ትእምት) ኩባንያዎች ዘንድሮ ከ16.5 ቢልዮን ብር በላይ የሚገመት ምርትና አገልግሎት ለገበያ ለማቅረብ እቅድ ተይዟል አለች።ለሲሚ ጀሮ እንዲጥም ግን አዜብ ከሁሉ አስቀድማ “የህዝብ ንብረት” ስትል የገለጸችውን ኤፈርት ባለፈው አመት ብቻ 376 ሚልዮን ብርበግብር ለመንግስት ገቢ አድርጓል አለች። ዋናውጥያቄ ደግሞ “የህዝብ ንብረት” ከሚሉ ቃላቶች ጋር ይሆናል። እውነት ኤፈረት የህዝብነውን? ከሆነ ታድያ ለምን በድብቅ በአንድ ቤተሰብ ቁጥጥር ስር ዋለ? የህዝብ ከሆነ ህዝቡ የማኔጅመንት ቦርድ አቋቁሞ በየጊዜውለምንየኤፈርት ገቢና ወጪአንዲያውቅ አልተደረገም?ከወ/ሮ አዜብ በፊት ኤፈርትን በሥራ-አስኪያጅነት ይዞ የነበረውየመለስ ታማኝ ካድሬ አባዲ ዘሞ (የአሁኑ በሱዳን የወያኔ አምባሳደር)መሆኑ ይታወሳል። ከአባዲ ዘሞ በፊት ኤፈረትን በመዳፉ አስገብቶ ይቆጣጠረው የነበረውሽማግሌውስብሃት ነጋ ነበር። ታድያ በሱ ጊዜበውጭየሚገኙ የህወሓት ደጋፊዎች መሃል ኤፈረት የህዝብ ነውከተባለ ለምን ኦዲት አይደረገም የሚልጭቅጭቅ ተነስቶ ኦዲት መደረግ
አለበት የሚሉ አሽንፈውየውጭአዲተር ቀጥረውወደ መቀሌ ይልካሉ። ወደ ኤፈረት ዋና ጽ/ቤት ያመራውየሂሳብ አካውንት መርማሪደግሞ ሽማግሌውን አግኝቶ ለምን እንደመጣ ሲነገረው፣ ስብሃት ነጋ ኃይለ-ቃል በተሞላበት አንደበት “በል ሌላ ችግር ሳይከተልህወደመጣህበት ቶሎ ተመለስ!” ብሎ አሰናበተው።

ወ/ሮ አዜብ ደግሞ ከኤፈርት የሚዘርፉት ገንዘብ አልበቃ ብሏቸውየትግራይን ህዝብ ከተቀረውወገኑ ጋር ለማጋጨት ድርጅቱን የፖለቲካመሳሪያ አድረገው ለመጠቀም እየተንቀሳቀሱ ያሉት። እዚህ ላይ አንዳንድ ተንኮሉ ያልገባቸውወገኖቻችን የአዜብን ቃል እንዳለ በመውሰድይኸው“እነኚህ ዘረኞች ትግራይን ለማልማት እንጂ” ቀሪውየኢትዮጵያ አካል ምናቸውም እንዳልሆን ነውየሚያሳየውእያሉ በጽሁፍሳይቀር ብሶታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ። ይኽም ማለት የነ በረከት/አዜብ አደገኛና ከፋፋይ ስትራተጂውጤትማ ሁኗል ማለት ነው።ምክንያቱም እነሱም ያቀዱት ፕላን ቢኖር፣ ተቃዋሚ ከሚባሉት ክፍሎች በኩል የሚሰነዘረውን አስተያየት ቀንጭቦ በመውሰድ፣ መልሰውለትግራይ ህዝብ “ይኸውእኛ ትግራይን በኢንዲስትሪ እናበለፅጋለን ስንል፣ ትምክህተኞችና ነፍጠኞች ግን ያንተን እድገት እየተቃወሙትይገኛሉ። እነዚህ ኃይሎችን ነውመፍራት ያለብህ። መድረክም ይሆን ሌሎች ተቃውሚዎች ጠላቶችህ መሆናቸውን ላንድ አፍታም ቢሆንመዘንጋት የለብህም!” እያሉ ህዝቡን ይበልጥ በወገኑ ላይ እንዲጠራጠር፣ ለውጥ ፈላጊ እንኳ ቢሆንም “ከማላውቀውመልአክ የማውቀውሰይጣን ይሻለኛል” ወደሚል ድምዳሜ እንዲደርስ ይገደዳል።

 ስለዚህ ወ/ሮ አዜብ ተናገረች ተብሎ እስዋን አምኖ፣ ነገሮችን በሰከነ አእምሮሳያጤኑ ወደ ድምዳሜ እና ወደ ማውገዝ መጓዝ የተቃዋሚውን ጎራ ትግል እንደሚጎድውና ይባስ ብሎ የገዢውን አካል እንደሚያጠናክር
ከወዲሁ መታወቅ ይኖርበታል።

ኢትዮጵያ በልጆችዋ የተባበረ ሃይል ታፍራና ተከብራ ትኖራለች!

ጋሻ ለኢትዮጵያውያን
ህዳር 14 2005
ሲያትል ዋሽንግተን

Saturday, December 1, 2012

EPRDF embroiled in Zenawi’s legacy Robele Ababya


Revelation of Zenawi’s vision for Tigray

Azeb Mesfin reportedly revealed the existence of a project document prepared by her late husband Zenawi to transform Tigray into an industrial center of the tribal-based Federation of Ethiopia. This rather surprising revelation and its timing has been a hot topic of debate with views converging on the question of what her husband’s vision was for the rest of the balkanized regions ofEthiopia.
Notwithstanding my record of advocacy for the development of Tigray, let me infer what traitor Zenawi had in mind for the rest ofEthiopia. In view of his intense hatred for the Amharas, Zenawi’s vision for the Amhara regional state could only be to relegate it to the role of supplying raw materials to the his envisioned industrial state of Tigray; the fate of Oromia region cannot be different for the strategy of the tyrant has all along been to emulate Mussolini’s policy to make the Amhara and Oromo major ethnic groups politically extinct – reduced to the level of consumers and providers of cheap labor as slaves and suppliers of their regions abundant natural resources as directed by their ruling masters. Prime Minister Desalegn Hailemariam, who has perhaps under duress allowed erosion of his power by unconstitutionally appointing two more Deputy Prime Ministers, has to inform the SEPDM Council about his predecessor’s ‘vision’ for the southern region.  One can only have sympathy for the humiliated PM.
Nightmarish issues for the EPRDF to resolve

The late tyrant Zenawi suddenly died mysteriously; the cause of his death has not been disclosed to date. His atrocious legacy has submerged his EPRDF Party in deep crisis.Ethiopiais on the threshold of catastrophe due to lack of an all-inclusive effective government amid brewing regional instability the Horn of Africa and souring relations withSudanandEgyptover theBlue NileRiver.

ወያኔ ታሪክን የማፍረስ ዘመቻውን ቀጥሏል!!

ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ ገና ከጫካ ሳይወጣ በስትራቴጂ ደረጃ የነደፈዉን ኢትዮጵያንና ታሪኳን የማጥፋት ዘመቻውን አሁንም እንደቀጠለ ነው። የወያኔ ዘረኞች የኢትዮጵያ ህዝብ የትግልና የመስዋዕትነት ምልክት የሆኑትን ጅግኖች ታሪክና የወያኔ አስራ ሰባት አመት የጫካ ትግል አሻራ ያላረፈባቸዉን ሰማዕታቶቻችንን የገድል ታሪክና ሀዉልት እያጠፋ በምትኩ የኔ ናቸዉ የሚላቸዉን የእነ አባ ጳውሎስን ዝከረ ሀውልትና የእነ መለስ ዜናዊን ምስሎች ብቻ በመዲናችን በአዲስ አበባ በማስቀረት፤ አዲስ አበባን የሀዝብ ሳይሆን የወያኔ ታሪክ ማስታወሻ እያደረጋት ነዉ። ወያኔ በላፈዉ አመት አጋማሽ ላይ በልማት ስም በታሪካዊዉ ዋልድባ ገዳም ላይ የጀመረዉን የአገር ታሪክና ቅርስ የማጥፋት ዘመቻ አሁን ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ አልበገረም ባይነት ታሪክ ተምሳሌት የሆኑትን የሰማዕቱን የአቡነ ጴጥሮስን ሀዉልት የባቡር ሀዲድ እሰራለሁ በሚል ሰበብ ለማፍረስ በዝግጅት ላይ ነዉ። ይህ የወያኔ የጥፋት ዘመቻ ደግሞ እኛ ካላቆምነዉ በቀር የማንነታችን መገኛ አረአያ የሆኑትንና የአበውን ጀግንነት፤ አልበገርም ባይነትና እምቢተኝነት የሚስታውሱን ግዙፍ የታሪክ ማስታወሻዎቻችን የወያኔ ቡልዶዘሮች ሰለባ የሚሆኑበት ቀን ሩቅ አይደለም። ይህን ዘረኛ አገዛዝ በቶሎ ማሰወገድ አለብን ሰንል ግባችን እድገትና ዲሞክራሲ ብቻ ሳይሆን በወያኔ እየላላ ያለዉን አንድነታችንን ማጥበቅና ወያኔ በየቀኑ እያወደመ ያለዉን የታሪክ ቅርሶቻችንን በፍጥነት ማዳንና መጠበቅ ጭምር ነዉ።
የጣሊያን ፋሺስቶች አቡነ ጴጥሮስን “አርበኞች የሀዝብና የአገር ጠላት” ናቸዉ ብለዉ የሚያስተምሩ ከሆነ ዛሬዉኑ ከእስር ይፈታሉ ሲሏቸዉ አምላኬ ይህንን አላስተማረኝም ብለዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ጠላቶች እነዚህ ፊት ለፊታችን የቆሙትና ከሩቅ አገር የመጡት ፋሺስቶች ናቸዉና የኢትዮጵያ ህዝብና መሬት ከእነዚህ ሀገር ቀሚዎች ስጦታ እንዳይቀበል” ብለዉ በህዝብ ፊት በጥይት ተደብድበዉ የሞቱ ጅግና ናቸዉ። ወያኔ የእኚህን ጀግና ሰዉ ታሪክ ሰበብ እየፈጠረ የሚያፈርሰዉ እንደም የእሱ አሻራ ስላላረፈበት በሌላ በኩል ደግሞ ህዝብ ይህንን ሀዉልት በተመለከተ ቁጥር የሚማረዉ አልበገርም ባይነትንና አልገዛም የሚል እምቢተኝነትን ስለሆነ ነዉ። ለዚህ ነዉ ወያኔ እንኳን በቁም ላሉት ሞተዉ ላንቀላፉት ጀግኖቻችንም የማይተኛዉ።  ወያኔን የመሰለ አገር በቀል ወራሪ ሀይልን ለአንዴና ለመጨረሻ እናጥፋ ሰንል እንደዚህ አይነቱን በማንነታችንና በታሪካችን ላይ የሚፈጸመዉን በደል ስር ከመስደዱና ትውልድን ከማጥፋቱ በፊት ለማስቆም ነዉ።
ወያኔ በተለመደ ቅጥፈቱ ሀውልቱ ተመልሶ ይመጣል እያለ የሚናገረው ህዝብን ለማዘናጋት እንጂ ከቶዉንም እውነቱን አይደለም፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ደግሞ እንደዚህ አይነቱን አይን ያወጣ ቅጥፍት ሃያ አንድ አመት ሙሉ አይቷል። ስለዚህ የኢትዮጵያ ህዝብ ይህንን ቅጥፈታቸውን ተረድቶ በምንም ነገር ሳይታለል አባቶቹ አስቀምጠውለት የሄዱትን የታሪክ አሻራዎች የመጠበቅ ግዴታ አለበት። የነጻነት ታሪክ አሻራና ቅርስን እያፈረሱ የሚሰሩት ልማት ከቶ ጥፋት እንጂ ልማት አይደለም። ትላልቅና አጅግ ዉስብስብ ለሆኑ ችገሮች መፍትሄ ያለዉ የምህንድስና ሙያ አዲስ አበባን ያክል ትልቅ ከተማ ዉስጥ አንድ ሳይሆን በብዙ ሺ የሚቆጠሩ መንገዶችንና የባቡር ሀዲዶችን የታሪክ ቅርሶቻችንን በማይነካ መንግድ እንዲሰሩ ማድረግ ይችላል። የአቡነ ጴጥሮስ ሀዉልት የቆመዉ አቡኑ ያንን ታሪካዊ ንግግር ባደረጉበትና ፋሽስቶች በጥይት በደበደቧቸዉ ቦታ ላይ ነዉና የኢትዮጵያ ህዝብ በእሳቸዉ ሀዉልት ላይ የተነጣጠረዉን የወያኔ ጠመንጃ ማክሸፍ ግዴታ አለበት።
ህወአት/ወያኔ ውብ ታሪካዊ ቦታዎችን፣ መታሰቢያ ቅርሶቻችንን ከኢትዮጵያ ህዝብ ታሪክ ጋር የተያያዙ ናቸዉ ያላቸዉን ቦታዎች ሁሉ ከኢትዮጵያ ካርታ ላይ  እየፋቀ የአምባገነኑን የመለስ ፎቶ፤ የአባ ጳዉሎስ ሀዉልትና የከሀዲ ጄኔራሎችን ምስል እያስቀመጠ ነዉ። በአጠቃላይ የወያኔ ዘረኞች እዉነተኛዉን የኢትዮጵያ ታሪክ በእነሱ የዉሸትና የፈጠራ ታሪክ እየተኩ ነዉ። ይህ የጥፋት ዘመቻቸዉ ስር ከሰደደና መጪዉን ትዉልድ በዚህ ጥፋታቸዉ እየበከሉ የሚያሰተምሩ ከሆነ ጥፋቱን ማረም እጅግ በጣም ይከብዳልና የኢትዮጵያ ህዝብ ነገ ዛሬ ሳይል ወያኔ በያዘው የጥፋት ዘመቻ ላይ ሆ! ብሎ በመዝመት ታሪካችንን ና ሀገራችንን ከወያኔ አምባገነኖች መንጋጋ ማስለቀቅ ወቅቱ የሚፈልገው ግድ ነው። ይህን ባለማድረጋችን ደግሞ የታሪክ ተጠያቂዎች ያደርገናል።
በመጨረሻም ወያኔዎች ሊረዱት የሚገባቸዉ አንድ ሀቅ ቢኖር ግዜና ትውልድ እንደሚፋረደቸውና የጀግናውና የታጋዩ አቡነ ጴጥሮስ ሀውልት በማፍረስ ሀውልቱን እንጂ እሳቸዉ የተሰዉለትንትን አላማ ከቶ ሊያፈርሱት እንደማይችሉ ነው። ይህ የሚያሳየን ገድለ-ታሪክ ታሪክን አምጦ ወልዶ በእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ልብ ውስጥ በጀግነነት ገድል ተጽፎ፣ ተቀልሞና ተከትቦ መቀመጡን ነው፤ ከዚህ በተጨማሪ ወያኔዎች ኢትዮጵያ ዉስጥ ብቻ ሳይሆን በመላው አፍሪካ ለዘላለም ሲከበር የሚኖርን ትልቅ የጀግንነት ስራ፤ ሀውልትን በማፍረስ ማጥፋት አንደማይችሉ ሊረዱ ያገባል እንላለን። ይልቁኑ ሃውልቱን ለማጥፋት የሚቆፈረው ጉድጓድ የወያኔ ማንነት የመጨረሻ መቀበሪያ የሚሆንበት ግዜ ሩቅ አለመሆኑን እያንድንዱ የወያኔ አባልና ደጋፊ አበክሮ ሊገነዘበዉ ይገባል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት ወታደራዊ ጥቃት ፈፀመ


በሰሜን ጎንደር መተማ ልዩ ስሙ ዘባጭ ባህር በተሰኘ ስፍራ ህዳር 20-2005 ከወያኔው የመከላከያ ሰራዊት ቅጥረኛ ጋር የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር አገር አድን ሰራዊትEthiopian People Patriotic Front ባካሄደው ውጊያ 13 /አስራ ሶስት/ የእብሪተኛው ቡድን ታጣቂዎች በመግደልና 17 /አስራ ሰባት/ በማቁሰል እንዲሁም ተተኳሽ መሳሪያዎችን በመማረክ ከፍተኛ ድል ተቀዳጅቷል።
በእለቱ በተካሄደው ውጊያ የወያኔው ታጣቂ ኃይል ተጨማሪ ሰራዊት በአካባቢው ያዘመተ ሲሆን፡ አርበኛው ሰሞኑን በተከታታይ እየወሰደ የሚገኘው ድንገተኛ ወታደራዊ ማጥቃት እርምጃ የህዝቡን ትኩረት ከመሳቡም ባሻገር በኢትዮጵያውያን ዘንድ የፀረ-ወያኔ ትግል መነሳሳት አብይ ሚና እየተጫወተ መሆኑን  በርካቶች እየገለጹ መሆኑም እየተገለጸ ነው።
የፖለቲካ ትግል የመጨረሻ አማራጭ የሆነው የትጥቅ ትግልን መፍትሄ አድርጎ ለአመታት ያህል የጊዜ፣ የእውቀት፣ የጉልበት ብሎም የህይወት መስዋዕትነት እየከፈለ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ኢትዮጵያን ከጎጠኛውና መሰሪው ኃይል የመከላከል አኩሪ ጥረቱን ዛሬም እንደ ትላንቱ ሳያሰልስ የሚገፋበት መሆኑን አስታውቋል።
ሰራዊቱ የተለመደውን ጀብድ በፈፀመበት አካባቢ የሚገኙ ነዋሪዎች የግንባሩን ሰራዊት እየተቀላቀሉ መሆኑን የገለጸው የድርጅቱ ወታደራዊ መምሪያ ግንባሩ በተከታታይ የወሰደውንና እየወሰደ የሚገኘውን  ወታደራዊ ማጥቃት የመላውን ኢትዮጵያ ህዝብ ድጋፍ የሚጠይቅ እንደመሆኑ መጠን ለሁለንተናዊ የአርበኝነት ትግሉ የተቻለውን በማበርከት ከስርዓት ለውጡ ተጠቃሚ የሚሆንበት አገር ለመገንባት መነሳት ይገባዋል የሚለውን መልዕክት  ያስተላለፋል።

ከፍተኛ ሙስና ፈጽመዋል የተባሉት ግለሰብ የኦሮምያ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ሆነው ተሾሙ


ኢሳት ዜና:-የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት ዛሬ ጉባኤውን ሲያጠናቅቅ የ77 ዳኞችን ሹመት አጽድቋል።የክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ሆነው የተሾሙት አቶ ፍቅሩ አያና ከምክር ቤት አባላቱ ከፍተኛ የሆነ ተቃውሞ ቢቀርብባቸውም፣ ከፍተኛ አመራሮች ስለፈለጉዋቸው ብቻ እንዲሾሙ መደረጉን የኦህዴድ ምንጮች ገልጸዋል።
የምክር ቤት አባላት በአቶ ፍቅሩ ላይ ካቀረቡዋቸው የመቃወሚያ ሀሳቦች መካከል ግለሰቡ በሙስና የተዘፈቁ ናቸው፣ በዞናቸው ዳኛ ሆነው በሰሩበት ወቅት በህዝብ የተጠሉና ህዝብን ያንገላቱ ናቸው፣ የስነምግባር ችግር አለባቸው፣ በህብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት የላቸውም የሚሉት ይገኙበታል። የክልሉ ባለስልጣናት ከምክር ቤት አባላት ለቀረበባቸው ተቃውሞ አጣርተን መልስ እንሰጣለን የሚል ድፍንፍን ያለመልስ በመስጠት ሹመቱ እንዲጸድቅ አድርገዋል።
የምክር ቤት አባላቱ በባለስልጣኑ አሰራር ላይ ነቀፌታ ሲያቀርቡ እንደነበር ታውቋል።
በጉባኤው ማጠናቀቂያ ላይ ክልሉን ፕሬዚዳንት አቶ አለማየሁ አቶምሳን ጨምሮ የስራ አስፈጻሚዎች የስልጣን ሹም ሽር ይኖራል የሚል አጀንዳ ተይዞ የነበረ ቢሆንም ምክንያቱ በውል ባልታወቀ ሁኔታ አጀንዳው እንዲሰረዝ ተድርጓል። መረጃዎች እንደሚያመለክቱት አቶ አለማየሁን ለመተካት ሀሳብ ቢቀርብም በሚተካው ሰው ላይ የስራ አስፈጻሚዎች ለመስማማት ባለመቻላቸው እንዲቀር ተድርጓል። አንዳንድ የስራ አስፈጻሚ  አባላት ስብሰባ ረግጠው እስከመውጣት መድረሳቸውን ለማወቅተ ችሎአል።
በሰሞኑ የምክር ቤት ስብሰባ ላይ አርብ እለት ከተገኙት ከምክትል ፕሬዚዳንቱ ከአቶ አብዱላዚዝ በስተቀር ፕሬዚዳንቱን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት በማጠቃለያው ጉባኤ ላይ አልተገኙም።
ሰሞኑን ለአቶ ሙክታር ከድር የተሰጠው የምክትል ጠቅላይ ሚኒሰትርነት ቦታ በተወሰነ መጠን በምክር ቤቱ ውስጥ ይነሳል ተብሎ የተጠበቀውን ተቃውሞ ማብረዱ ታውቋል።
በሌላ ዜና ደግሞ አዳማ 5ኛውን ከንቲባ ሾማለች። ከሙስና ጋር በተያያዘ ከህዝብ በቀረበ ተቃውሞ ከስልጣን እንዲባረሩ በተደረጉት የተወካዮች ምክር ቤት አባሉ በአቶ ጉታ ላንጮሬ በአቶ ባካር ሻሌ ተተክተዋል። አቶ ባካር ሻሌ አቶ በረከት የሚመሩት የኮሚኒኬሽን ጽህፈት ቤት ምክት ሃላፊ የነበሩ ናቸው።
አንዳንድ ወገኖች ግለሰቡ በእርግጥም ከሙስናና ከአስተዳደር ብቃት ጋር በተያያዘ በከተማው ህዝብ ዘንድ ተቃውሞ ተነስቶባቸው የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ከስልጣናን የተባረሩት ግን ምናልባትም በኦህዴድ ውስጥ ከተፈጠረውን ችግር ጋር ተያይዞ ሊሆን እንደሚችል ይናገራሉ።
ኢሳት የከንቲባውንና የከተማ ልማት ቢሮ ሀላፊውን ከስልጣን መባረር መዘገቡ ይታወሳል።